ኔፕፕላስ አዲስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ሾመ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን አትዮጵያ (ኔፕፕላስ) አዲስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ሾመ፡፡ የኔፕፕላስ ስራ አመራር ቦርድ የካቲት 1 አና 2 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ባካሄደው ስብሰባ ከቀረቡት አጩዎች መካከል አቶ ካሳሁን ታደሰን ባላቸው የስራ ልምድ፤ ክህሎት እና ብቃት ለቦታው ብቁ መሆናቸውን በማረጋገጡ የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟል፡፡ የኔፕፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱረሃማን ከማል እንደገለጹትም ለቦታው ከቀረቡት እጩዎች መካከል አቶ ካሳሁን ድርጅቱን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርጉት በመተማመን የስራ አመራር ቦርዱ በሙሉ ድምጽ የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟቸዋል፡፡

አቶ ካሳሁን ታደሰ አዲሱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር

አቶ ካሳሁን ታደሰ የትምህርት ዝግጅታቸውን ስንመለከት የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በማኔጅመንት ያገኙ ሲሆን፤ በቢዝነስ ደግሞ የማስተርስ ድግሪያቸውን ሰርተዋል፡፡ በተጨማሪም በፐብሊክ ኸልዝ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እና ጥናቶችን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ አቶ ካሳሁን በስራው አለም በአጠቃላይ ወደ 17 አመታት ልምድ ያላቸው ሲሆን፤ ከእንዚህ ውስጥም ዋና ዋናዎቹ የኢትዮ ላይፍ ሴቪንግ አሶሲየሽን መስራች እና ጀነራል ማናጀር ሲሆኑ በተለያዩ ትላልቅ ድርጅቶች ውስጥም በተለያየ የሃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል፡፡ ከእንዚህ ተቋማት መካክልም በኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ በኤክስኮዩቲቭ ዳይርክተርነት እንዲሁም በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማናጀርነት ፤ በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ አይ ካፕ ኢን ኢትዮጵያ በአድሄረንስ ሰፖርተርነት አማካሪ እና አድሄረንስ ኬዝ ማናጀመንት ፕሮግራም ኤክስፐርት ናቸው፡፡

ለዚህ ሃላፊነት መመጣቸውን ተከትሎ ድርጅቱን አሁን ካለበት ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የአጭር ጊዜ እቅዶችን መያዛቸውን የገለጹልን አቶ ካሳሁን ፤ ይሄንን ለማሳካተም የድርጅቱን የውስጥ አቅም ማደራጀት፤ የኔትዎርኩንና የክልል ኔትዎረኮችን አቅም በቴክኒክ፤ በእውቀት እንዲሁም በክህሎት ማጠናከር፤ ከለጋሾችና ከአጋር ደርጅቶች ጋር የነበረውንና የተቋረጠውን ግንኙነት መልሶ በማስቀጠል ሃብት የማበልጸግ ስራዎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ገልጸውልናል፡፡ ኔፕፕላስ ምንም እንኳን እውቅና የተሰጠው ትልቅ ድርጅት ቢሆንም በመንግስት በኩል እስካሁን ድረስ ፋይል ያልተከፈተለት በመሆኑ በቀጣይ ግን ፋይል ተከፍቶለት ጤና ሚኒስቴር በየአመቱ ከሚመደብለት በጀት ላይ አመታዊ በጀት እንዲመድብለት ለማድረግ በርካታ ስራዎችን የመስራት እቅድ እንዳላቸው እንዲሁም የደርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ፤ ፖሊሲ እና ስትራቴጂክ ፕላን ዘመኑን በዋጀ ምልኩ የመከለስ እና የማዘጋጀት ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል አቶ ካሳሁን፡፡

ምንም እንኳን እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን ለማከናወን በከፍተኛ ዝግጅት የመጡ ቢሆንም የተወሰኑ ተግዳሮቶች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ የገለጹት አቶ ካሳሁን፤ እነዚህን ችግሮች በተገቢው መንገድ ለመቋቋም መዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል፡፡ የመጀመሪያው ሊገጥም የሚችለው ተግዳሮት የታሰበውን እና አስፈላጊውን ያህል ሃብት የማግኘት ችግር ሲሆን፤ ይሔ ችግርም በተለያየመልኩ ይፈታል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በድርጅቱ ውስጥም ሆነ በክልል ኔትዎርኮች ውስጥ ያለውን የጥቅም ግጭት ለመፍታት በቴክኒክ፤ በእውቀት እና በክህሎት የአቅም ማጎልበት ስራዎች ይሰራሉ እንደ አቶ ካሳሁን ገለጻ፡፡ ሌላው ሊገጥም ይችላል ያሉት ተግዳሮት ለጋሾች በየጊዜው መቀያየራቸው የየራሳቸውን ባሕሪ ይዘው ስለሚመጡ ያንን ጫና ለመቋቋምና ተመቅረፍ የሃገር ውስጥ ሃብት የማፈላለግ ስራም ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ክልሎች የተመደበላቸውን ሃብት በእግባቡ አለመጠቀም ሌላው ሊገጥም የሚችል ተግዳሮት መሆኑን የገለጹት አቶ ካሳሁን ይሄንንም በተለያየ መንገድ ለመቅረፍ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ኔፕፕላስ በሃገር አቀፍ ደረጃ ቫይረሱ ያለባቸውን በርካታ ወገኖች ያቀፈ ዣንጥላ አንደመሆኑ የግል ጥቅምን ሳይሆን የማህበረሰቡን ድምጽ ለማሰማት እና ቫይረሱ ያለባቸው ወገኖች የተሻለ ህክምና በማግኘት የተሻለ ህይወት እንዲኖሩ የሚረዳ፤ በመንግሽጽና በኅዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የመንግስትንም ጫና የሚቀንስ ሃገር አቀፍ ድርጅት እንደመሆኑ; ሁሉም አካል በእኔነትና ይመለከተኛል በሚል ስሜት እጅና ጓንት ሆኖ በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሁሉም በኔትዎርኩ ዙሪያ ያለ አካል አንድ በመሆን የግል ስሜትን ሳይሆን የማህበረሰቡን ጥቅም በማስቀደም እና በአገልጋይነት ስሜት ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም መክረዋል፡፡

በየጤና ተቋማት የሚሰሩ ኬዝ ማናጀሮች እና የአድሄረንስ ሰፖርተሮች በመንግስት መዋቅር እንዲካተቱ ሃሳብ ቀረበ

የኤች አይ ቪ ስርጭትን በመግታት እቅስቃሴ ውስጥ ላለፉት 11 አመታት ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የነበሩት ኬዝ ማናጀሮች እና የአድሄረንስ ሰፖርተሮች አስፈላጊነት ላይ ያተኮረ ዎርክሾፕ በቢሾፍቱ ከተማ ከመስከረም 10 – 11 ቀን፤ 2015 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ በውይይቱ መጨረሻም ሰራተኞቹም በመንግስት አስተዳደር ኮሚሽን እንዲታቀፉ ሃሳብ ቀርቀቧል፡፡ በዎርክሾፑ ላይም የኔፕ ፕላስ ቦርድ አባላት ፤የፌድራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተወካዮች ፣ የጤና መድህን አገልግሎት ባለሞያዎች ፤ የጤና ሚኒሰቴር ተወካዮች ፤ የክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተወካዮች፤ የየክልል ጤና ቢሮዎች ተወካዮች፤ አንዲሁም የተለያዩ አካላት ተሳትፈዋል፡፡


የዎርክሾፑ ተሳታፊዎች በከፊል
በዎርክሾፑ መክፈቻ ላይ የኔፕፕላስ ተ/ዳይሬክተር አቶ ባይሳ ጫላ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ኔፕፕላስ ባለፉት 11 አመታት ኤች አይ ቪ በደማቸው ያለባቸውን ዜጎች በማሰማራት በተለያየ መልኩ ህብረተሰቡን የጠቀመ መሆኑን አስረድተው፤ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ለምሳሌ የሚቀርቡ ናቸው ብለዋል፡፡ አሁንም ሲዲሲ ለዚህ ስራ ይሰጠን የነበረው በጀት ቢያቆምም በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አቶ ባይሳ በንግግራቸው አንስተዋል፡፡

በአሁን ወቅት በሃገሪቱ ያለውን የኤች አይ ቪ ሁሄታ በተመለከተ የጤና ሚኒሰቴርን ወክለው ጽሁፍ ያቀረቡት አቶ ደስታ ሞገስ ሲሆኑ፤ በጽሁፋቸውም በየአመቱ ከ 1ነጥነብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በኤች አይ ቪ ቫይረስ የሚያዙ ሲሆን፤ በዚሁ ምክንያትም 680 ሺ ዜጎች ህይወታቸው ያልፋል ብለዋል፡፡ በቀረበው ጽሁፍ እንደተቀመጠው ከእነዚህም ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ሴቶች ሲሆኑ፤ በዚህም መሰረት 19 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሴቶች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኘ ተገልጿል፡፡ የወንዶችን ቁጥር ስንመለከት ደግሞ 16 ነጥብ 7 ሚሊዮን ወንዶች የኤች አይ ቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ይገኛል፤ እንደ ጽሁፉ፡፡ በኤች አይ ቪ ቫይረስ ምክንያት የሚሞቱ ወገኖች ቁጥርን ስንመለከትም በቀላሉ የሚታይ አይደለም ያሉት አቶ ደስታ፤ በዚሁ ምክንያት በየአመቱ 640ሺ ወንዶች እና 240 ሴቶች ህይወታቸው ያልፋል ብለዋል፡፡
የቫይረሱን ስርጭት በእድሜ ስብጥር ስንመለከተው በ2021 በነበረው መረጃ መሰረት በየአመቱ አድሜያቸው ከዜሮ እስከ 14 አመት የሆነ 150 ሺ ህጻናትና ታዳጊዎች በቫይረሱ የሚያዙ ሲሆን፤ በዚሁ ሳቢያም 99ሺ ሕጻናትና ታዳዎች በሞት ይቀጠፋሉ፡፡ በክልል ደረጃ ያለውን የቫይረሱን ስርጭት በተመለከተም መረጃው እንዳስቀመጠው በ2021 አማራ ክልል፤ ኦሮሚያ እንዲሁም አዲሰ አበባ በቅደም ተከተል ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ካደረጉት ምክንያቶች መካከልም በተለይ ሴቶች ስለቫይረሱ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ መሆን፤ ኮንዶምን በአግባቡ አለመጠቀም፤ ጾታን መሰረት ያደረጉ ተግባራት አሁንም ድረስ እየተተገበሩ መሆኑ እንዲሁም የወሲብ ንግድ መስፋፋት ናቸው፡፡
የአቶ ደስታን ማብራሪያ ተከትሎ የኔፕፕላስ ፐሮገራም ማናጀር አቶ ድንቁ ወርቁ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ምንነት እና አስፈላጊነት የሚገልጽ ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፤ በጽሁፋቸውም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በጤና ተቋማት እና በማህበረሰቡ መካከል የሚኖረው አገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን ከፍተኛውን ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በማህበረሰቡ እና በጤና ተቋማት ዘንድ ያለውን ሀብት በአግባቡ አሟጦ መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያላቸው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑ አብራርተዋል፡፡ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች ዋና ዋናዎችም ዜጎች የኤች አይ ቪ ምርመራ እንዲያደርጉ የምክር አገልግሎት መስጠት ፤ ከራሳቸው ተሞክሮ ተነስተው ያለውን ሁኔታ በግልጽ በማስረዳት ቫይረሱ በደማቸው ያለ ዜጎች ህክምና እንዲጀምሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ህክምናውን ያቋረጡ ዜጎች ወደ ህክምናው እንዲመለሱ የተለያዩ ጥረቶችን ማድረግ ተጠቃሾች መኆናቸን አቶ ድንቁ ጨምረው አብራርተዋል፡፡

የዎርክሾፑ አወያዮች

ሌላው የኬዝ ማናጀሮችና ደሄረንስ ሰፖረተሮች ስራ ያስገኛቸው ውጤቶችና የጋጠሙ ችግሮችን በተመለከተ ጽሁፍ ያቀረቡት የኔፕፐላስ ምዘናና ግምገማ ባለሞያ አቶ ቢኒያም ወርቁ ሲሆኑ፤ በጽሁፋቸውም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሚሰሯቸው ስራዎች በርካቶች ቫይረሱ በደማቸው ያለ ዜጎች ህክምናቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ እና ህክምና ባለማግኘታች ሊደርሱ የሚችሉ ችግሮችን ማስቀረት መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ለአብነት ያህልም በ2020 እና በ2012 ብቻ ህክምናቸውን ካቋረጡ ከ80ሺ በላይ ወገኖች መካከል ከ40ሺ በላይ የሚሆኑት ወደ ህክምና እንዲመለሱ ማድረግ ችለዋል ብለዋል አቶ ቢኒያም ፡፡በተጨማሪም በኬዝ ማናጀሮች እገዛ እየተደረገላቸው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸው የኤች አይ ቪ ምርምራ እንዲያደርጉ በማሳመን እና ወደ ምርመራ ቦታ በማምጣት ሥራው ላይ እንዲሳተፉ ማድረጋቸውን አቶ ቢኒያም በማብራሪያቸው ገልጸዋል፡፡
የኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖረትሮች የሚሰጡት አገልግሎት በርካታ ቢሆንም፤ ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይወጡ የሚደርጓቸው በርካታ ችግሮች መኖራቸውንም አቶ ቢኒያም አስረግተዋል፡፡ ከእነዚህ ችግሮች መካከልን እንደ እሳቸው ገለጻ ዋና ዋናዎቹ የምክክር አገሎገሎት ለመስጠት የሚመቹ ገለልተኛ ክፍሎች አለመኖር፤ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰርቪስ ስር ባለመታቀፋቸው ልዩ ልዩ ጥቅማ ጥቅሞች ማግኘት አለመቻላቸው፤ ከጤና ተቋማት ደጋፍ በተገቢው መንገድ ማግኘት ነጻ ህኪምና ማግኘት አለመቻላቸው እንዲሁም ዝቅተና ደመወዝ ተከፋይ መሆናቸው እና የፕሮጀከቶች ስራ በጊዜ የተገደበ መሆን ተጠቃሾቹ ናቸው ብሏል አቶ ቢኒያም፡፡
ከየተቋማቱ የመጡ ተሳታፊዎች በየዘርፋቸው 20 የደቂቃ ገለጻዎችን ያደረጉ ሲሆን፤ በዋናነት ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮችም የኤች አይ ቪ አሁናዊ ተጨባጭ ሁኔታ፤ የኬዝ ማናጀሮች አስፈላጊነት፤ የሚሰሯቸው ስራዎች አንዲሁም ስራዎቻቸውን በሚሰሩበት ወቅት የሚገጥሟቸው ችግሮች አና ችግሮቹን ለመፍታት የተጓዙባቸውን መንገዶች የሚያስረዱ መረጃዎች ለተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡
ከዚህ በመቀጠልም እያንዳንዱ ክልል የየራሱን ተሞከሮ ያቀረበ ሲሆን፤ የአማራ ክልል ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰርቪስ ስር እንዲካከቱ በማድረጉ ችግሩን ከሞላ ጎደል መቅረፍ መቻላቸውን ተወካዩ አስረድተዋል፡፡ ሌሎችም በቀጣይነት ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰረቪሱ ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወገኖች በጤና መድህን ሊታቀፉ የሚችሉበት እና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት በሚቻልበት መንገድ ላይም ማብራሪያ ቀርቧል፡፡ ከኢትጵያ ጤና መድን አገልግሎት ተወካይ አቶ ጉደታ አበበ በአሁኑ ወቅት ያለውን የጤና መድን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ እንደ አቶ ጉደታ ማብራሪያ የጤና መድን አገልግሎት ለሁሉም ዜጋ መዳረሱ እንደ ግዴታ ሊወሰድ ስለሆነ ማንም ከዚህ አገልግሎት ውጪ ሊሆን አይችል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉም ዜጋ በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድን አሊያም በማህበራዊ ጤና መድህን እንዲታቀፍ የሚያስገድድ ህግ ተግባራዊ ሥለሚደረግ በዚህ ሂደት ውስጥ ቫይረሱ በደማቸው ያለባቸው ዜጎችም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አቶ ጉደታ ጨምረው አስረድተዋል፡፡
በውይይት መድረኩ በተለይ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች የቫይረሱን ስርጭት በመግታት ረገድ ያላቸው ጠቀሜታ የጎላ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ በሲቪል ሰርቪሰና በጤና መድን ስር ታቅፈው አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ እና እያንዳንዱም የየራሱን ሃላፊነት ለመወጣት ቃል በመግባት ስብሰባው ተጠናቋል፡፡

አድሎና ማግለል ጥናት ላይ ውይይት ተካሄደ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭሰ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) በመድሎና ማግለል ላይ
ከህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጋር ውይይት አካሄደ
ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) በኤች
አይ ቪ ምክንያት በሚደርሰው አድሎና ማግለል ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማህበራዊ
ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴጋር ነሃሴ 2 ቀን 2014 በቢሾቱ ኪሎሌ ሆቴል ውይይት አካሂዷል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይም የተለያዩ አካላት ንግግር አድርገዋል፡፡


የውይይቱ ተሳታፊዎች በከፊል

በውይይቱ ቋሚ ኮሚቴውን በመወከል ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ ሲሆኑ፤
እሳቸውም በገለጻቸው በኤች አይ ቪ ተጽእኖ ላይ እንዲህ አይነት በቁጥር ላይ የተመሰረተ
ጥናት መቅረቡ በጉዳዩ ላይ የበለጠ ስራዎችን ለመስራት የሚኖረው ጠቀሜታ የላቀ መሆኑን
አብራርተዋል፡፡ በግምት ብቻ የሚሰሩ ስራዎች የተፈለገውን ውጤትለማስገኘትም ሆን
በህብረተሰቡ ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚደረገው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ይፈጥራል
ብለዋል ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ ፡፡ በዚህ መልኩ ተጨባጭነት ያለው ጥናት መደረጉ በጉዳዩ
ላይ የበለጠ ለመስራት የሚፈልግ ሌላ አካል እንኳን ቢኖር ጥሩ መነሻ የሚሆንና
በማህበረሰቡ ውስጥም ለውጥ ለማምጣት የሚያግዝ መሆኑን ወ/ሮ ወርቅሰሙ ጨምረው
ገልጸዋል፡፡


ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ
ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ተወክለው የመጡት ወ/ ሮ ምርቴ ጌታቸው በበኩላቸው ሚኒስቴር
መስሪያ ቤቱ የኤች አይ ቪ ስርጭት አና የሚከሰቱት ተያያዥ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ብዙ
ስራዎችን እየሰራ መሆኑን በመግለጽ፤ እንዲህ አይነት ጥናቶች መካሄዳቸው ስራውን የበለጠ
ለማቀላጠፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አብራርተዋል፡፡ ባለፉት አመታት በኤች አይ ቪ
ምክንያት የሚከሰት ሞትን በ 53በመቶ እንዲሁም የቫይረሱን ስርጭት 87 በመቶ መቀነስ
ተችሏል ያሉት ወ/ሮ ምርቴ፤ የኤች አይ ቪ ህክምና ሽፋኑ 93 በመቶ እንዲሁም ቫይረሱን
የመቆጣጠር አቅም ወደ 96 በመቶ ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል ተወካዩዋ፡፡ ተመርምሮ
ራስን ማወቅን በተመለከተም በአሁኑ ወቅት 84 በመቶ የሚሆኑት ወገኖች ተመርምረው
ውጤታቸውን ያወቁ ሲሆን፤ በተቃራኒው ደግሞ 16 በመቶ የሚሆኑት በተለያዩ ምክንያቶች
ምርመራ እንዳላደረጉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ተመርምረው ራሳቸውን እንዳያውቁ
ከሚያደርጓቸው ምክንያያቶች መካከልም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሊደርስባቸው
የሚቸለውን መድሎና መገለል በመፍራት መሆኑንም አብራርተዋል ፡፡ በአሁኑ ሰአትም ከ
1500 በላይ የሚሆኑ የኤች አይ ቪ ህክምና መስጫ ጣቢያዎች እንዲሁም ከ4000 በላይ የ
ኤች አይ ቪ የምርመራ ጣቢያዎች እንዳሉም አብራርተዋል ወ/ሮ ምርቴ፡፡


ወ/ሮ ምርቴ ጌታቸው

እንግዶች ያደረጉትን ንግግር ተከትሎም የጥናቱን አስፈላጊነት፤ አላማ እና አካሄድ
በተመለከተ የኔፕ ፕላስ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የጥናቱ የቴክኒክ ኮሞቴ ሰብሳቢ አቶ
ጌታቸው ጎንፋ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ጥናቱን ማድረግ የተፈለገበት
ምክንያት በኤች አይ ቪ ምክንያት የሚደርስ መድሎና መገለል ያለበትን ደረጃ አና ሁኔታ
ለማውቅ ፤ በመድሎና መገለል እና በኤች አይ ቪ አገልግሎት መካከል ስላለው ግንኙነት
ለመገምገም እንዲሁም በመድሎና መገለል ምክንያት የሚደርሰውን አሉታዊ ተጽእኖ ማቃለል
በሚቻልበት ሁንታ ላይ ምክረ ሃሳብ ለማስቀመጥ እንደሆነ አቶ ጌታቸው በገለጻቸው
ጠቁመዋል፡፡
የዳሰሳ ጥናቱን ለማድረግም የተለያዩ አባላት ያሉት ኮሚቴ ተዋቅሮ እንደነበረ እንዲሁም
በሂደቱ የተለያዩ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ዘዴዎች መከተላቸውን ገልጸዋል፡፡ ጥናቱ
ደረጃውን የጠበቀ እና ተአማኒነት ያለው እንዲሆንም በዘርፉ ልምድ ያላቸው የጥናት ተቋማት
ያስቀመጧቸውን ያሰራር ሂደቶች በመመልከት እና በመከተል መሰራቱም በመድረኩ
ጨምረው አብራርተዋል፡፡

አቶ ጌታቸው ጎንፋ
በመቀጠልም የጥናቱ ቴከኒካል ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩዬ
ዳመጠው አጠቃላይ የጥናቱን ውጤት ጠቅለል ባለ መልኩ አቅርበዋል፡፡ በማብራሪያቸወም
ከጠናቱ ተሳታፊዎች መካከል ምን ያህሉ የኤች አይ ቪ ውጤታቸውን ለሌሎች አካላት
አሳውቀዋል በሚል የጀመረው የወ/ሮ ጥሩዬ ገለጻ፤ በዚህ ጥናት ላይ ከተሳተፉ ሰዎች መካክል
84 በመቶዎቹ የኤች አይ ቪ ውጤታቸውን ቢያንስ በአካባቢያቸው ለሚገኝ አንድ ሰው
መግለጻቸውን ያመለክታል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ 16 በመቶ የሚሆኑት የኤች አይ ቪ
ውጤታቸውን ለማንም ሰው ያልገለጹ መሆናቸውን ምክትል ሰብሳቢዋ አክለው ገልጸዋለ፤፡፡
በተጨማሪም 23.4 በመቶዎቹ የጥናቱ ተሳታፊዎች የ ኤች አይ ቪ ውጤታቸው
ያለፍቃዳቸው የተገለጸባቸው ፤ 19.7 በመቶዎቹ ደግሞ የ ኤች አይ ቪ ውጤታቸውን
ያሳወቁት በተለያዩ ምክንያቶች ተገደው እንደሆነ የጥናቱ ተሳታፊዎች መግለጻቸውን
አብራርተዋል፡፡ ውጤታቸውን ይፋ እንዲያደርጉ ያሰገደዷቸው ነገሮችም የፍቅር እና የትዳር
ጓደኛ ለመያዝ፤ የተለያዩ እገዛዎችን ለማግኘት አና ለመሳሰሉት ምክንያት እንደሆነ የጥናቱ
ተሳታፊዎች አብራርተዋለ፡፡

ወ/ሮ ጥሩዬ ዳምጠው
የቀረበው መረጃ እንደሚጠቁመው በ ኤች አይ ቪ ምክንያት የሚመጣ መድሎና
መገለል ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ዜጎች ላይ አዎንታዊ አና አሉታዊ ተጽእኖዎችን
ያስከትላል፡፡ 45 በመቶ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች እንደገለጹትም በኤች አይ ቪ
ውጤታቸው ምክንያት የደረሰባቸው መድሎና መገለል በሕይወታቸው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ
አሳደሮባቸዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ እንደገለጹትም በተደረገባቸው መድሎና መገለል ሳቢያ በራስ
መተማመናቸውን እንዲያጡ፤ ጭንቀትን መቋቋም እንዲያቅታቸው ብሎም የፍቅር ጓደኛ
እንኳን መያዝ እንዳይችሉ አድርጓቸዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ልጅ ለመውለድ
የነበራቸውን ተስፋ እንዳሳጣቸው ገልጸዋል ተብሏል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ 44 በመቶ
የሚሆኑት ተሳታፊዎች በ ኤች አ ይ ቪ ውጤታቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ያለው
መድሎና መገለል የበለጠ በራሳቸው አንዲተማመኑ በማድረግ፤ ጭንቀታቸውን እንዲቋቋሙ
በማገዝ እንዲሁም ጠንካራና ተስፈኛ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ በአዎንታዊ መንገድ
እንደረዳቸው ተጠቁሟል፡፡
የጥናት ውጤቱ አጠቃላይ ዳሰሳ ከቀረበ በኋላም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች አና
አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን፤ ለጥያቄዎቹ ምላሽ እና ማብራሪያዎች ከአቅራቢዎች
ተሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ተሳታፊዎች የየራሳቸውን አስተያያት አና ጥቆማ በመስጠት እና
ሰፊ ውይይት በማድረግ የውይይት መድረኩ ተጠቃሏል፡፡

የኔፕ ፕላሰ 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ

የኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕ ፕላስ) 17ኛ
መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ግንቦት 1 እና 2 ቀን 2014 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ከረዩ ሂል ሪዞርት
ሆቴል ተካሂዷል፡፡
በጉባዔው መክፈቻ ላይ የኔፕ ፕላስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ባይሳ ጫላ ባደረጉት ንግግር፤
ኔፕ ፕላስ ላለፉት 17 አመታት ከተለያዩ አካላት ጋር በመቀናጀት ከ200 ሺህ በላይ ቫይረሱ
በደማቸው የሚገኝ ወገኖች በማህበር ተደራጅተው አድሎና መገለል እንዲቀንስና ለሀገራዊ
ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ፤
ማህበረሰቡም ራሱንና ቤተሰቡን ከወረርሽኝ እንዲጠብቅ እንዲሁም እንደአስፈላጊነቱ ራሳቸውን
ይፋ በማውጣት ትምህርት እንዲሰጡ የማድረግ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በ 2030 ሊደርስበት ያስቀመጠውን የ 95 ፤ 95 ፤ 95 እቅድ
ተግባራዊ ለማድረግ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወገኖች ከጸረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት ጋር
እንዲቆራኙ ወይም የህክምና ክትትላቸውን እንዲያጠናክሩ እንዲሁም መድሃኒቱን ጀምረው
ያቋረጡ ወገኖች በአፋጣኝ ወደ ህክምና ክትትል እንዲመለሱ የማድረግ ስራ በመሰራት ላይ
ይገኛል ብለዋል አቶ ባይሳ፡፡
የኔፕፕ ፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብድርሃማን ከማል በበኩላቸው፤ ለአዲሱ
የግሎባል ፈንድ ውድድር በቂ ዝግጅት በማድረግ ውጤታማ ሆኖ ለማሸነፍ መቻሉን
አብራርተዋል፡፡ ከአለፈው ጠቅላላ ጉባዔ ወዲህ ባለው ስራቸው ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን
ሰብሳቢው ሲገልጹም ፤ ወቅቱን ያልጠበቀ የሲዲሲ በጀት መቋረጥ፤ በርከት ያሉ ሰራተኞች
ስራቸውን መልቀቅ እና የበጀት እጥረት ዋናውናዎች መሆናቸውን አስቀምጠዋል፡፡ እነዚህን
ቸግሮችም በተለያየ መልኩ ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች መደረጋቸውን ሰብሳቢው ጨምረው
ገልጸዋል፡፡ የስራ አመራሮችን በተመለከተም የአመራርነት ሃላፊነታቸውን ያልተወጡትን
የብሄራዊ ጥምረቱ ስራ አስኪያጅ በአዲስ ተወካይ ቦርዱ መተካቱን ሰብሳቢው ጨምረው
ገልጸዋል፡፡
የበመቀጠል ጠቅላላ ጉባዔው የተጓደሉ እና ጊዜያቸውን የጨረሱ የጠቅላላ ጉባዔ
አመራሮች ምርጫ በህገ ደንቡ መሰረት አካሂዷል፡፡ ጉባዔው በሶስቱ አስመራጭ ኮሚቴ
አባላት አማካይነት አዲስ አመራሮችን የመረጠ ሲሆን፤ በዚህም መሰረት አቶ ማሙሸ ንጉሴ
የጠቅላላ ጉባዔ ሰብሳቢ ፤ወ/ሮ እቴነሽ እሸቴ የጠቅላላ ጉባዔ ም/ሰብሳቢ እንዲሁም አቶ ሙሴ
ማማጫ የጠ ቅላላ ጉባዔ ጸኃፊ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
በተጨማሪም በድርጅቱ በቦርድ አባልነት ከሀረሪ ክልል፤ ከአዲስ አበባ እና ከሴቶች
ጥምረት የተወከሉትን 3 የክልል ተወካዮችን ጉባዔው በቦርድ አባልነት እንዲሰሩ ጉባዔው
ያጸደቀ ሲሆን፤ በተገጓደሉ ጠቅላላ ጉባዔ አባልነትም የጋመቤላ ክልል ወክሎ የላከው 1፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የላካቸው 2 እና ሴቶች ጥምረት የላካቸው 4 ተወካዮችን
አጽድቋል፡፡
ጠቅላላ ጉባዔው በመቀጠልም በ2021 የተሰሩ ስራዎችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን፤
በመጀመሪያ የስራ አመራር ቦርዱን ሪፖርት በዝርዝር አይቷል፡፡
በቦርዱ ሪፖርት ላይ ከአባላት የተለያዩ ጥያቄናዎችና አስተያቶች የተነሱ ሲሆን፡
ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የቦርዱ ሰብሳቢው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡ ሰብሳቢው
በምላሻቸውም የተቋረጠውን የሲዲሲ ፕሮጀክት በተመለከተ ፕሮጀክቱን ለመመለስ ጥረት
እንደሚደረግ፤ የኔፕ ፕላስ በጀት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ በመሆኑ የድርጅቱ መመሪያዎችና
ደንቦችን በዚያ መልኩ እንደሚቃኝ አስረድተዋል ፡፡ የግሎባል ፈንድ አሰራሩ በአጠቃላይ
ስለተቀየረ የበጎ ፈቃደኞችን እና ሌሎች ሰራተኞችን አለማካተቱን የገለጹት ሰብሳቢው፤
በተጨማሪም በጦርነት የተጎዱ ክልሎችንና ሌሎች ድጋፍ የሚፈልጉ ማህበራትን ለመደገፍ
ቦርዱ ከ ጽ/ቤቱ ጋር የጋራ እቀድ አቅዶ እንደሚንቀሳቀስ ገልጸዋል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው ቦርዱ
ስራውን በአግባቡ እያከናወነ መሆኑን የተገነዘበ ሲሆን ፤ ለሚቀጥለው አመት የሃብት ማበልጸግ
ስራ እንዲሁም የውጪ የቦርድ አባላትን የማካተቱ ስራ ትኩረት ተሰጠቶ እንዲሰራ የውሳኔ
አቅጣጫ ሰጥቷል፡፡
ቀጥሎ ለጠቅላላ ጉባዔው የጽ/ቤቱ የ2021 ሪፖርት በክትትልና ምዘና መምሪያ ሃላፊው
በአቶ በላይ ረታ የቀረበ ሲሆን ፤ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ በላይ
ማብራሪያ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል ከ 150 ሺህ በላይ ለሆኑ ቫይረሱ በደማቸው ላለባቸው
ወገኖች በጸረ ኤች ኤቪ ህክምና ቁርኝት፤ በቫይረስ መጠን ልኬት ፤ በጸረ ኤች አይቪ ህክምና
ቅድመ ዝግጅት፤ ቤተሰብና የጾታ አጋሮቻቸውን በማስመርመር ፤ ከኮቪድ 19 በመከላከል እና
በአጠቃላይ ጤና አጠባበቅ ዙሪያ የግንዛቤ ማዳበሪያ ድጋፍ እንደተሰጣቸው ተብራርቷል፡፡
ከቀረበው ሪፖርት መረዳት እንደተቻለውም ድርጅቱ በኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት መቀነስ እና
መድሎና መገለል እንዲቀንስ በማድረግ እንዲሁም ከጸረ ኤች አይቪ መድሃኒት ጋር ያለውን
ቁርኝት በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡
አባላቱ ሪፖረቱ ካደመጡ በኋላም ፈንድ ለማግኘት ከመንግስት ጋር ያለው ቁርኝት ምን
ይመስላል፤ እንዲሁም የኔፕ ፕላስ የ 5 አመት መሪ እቅድ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ የሚሉና
የመሳሰሉ ጥቄዎችን አንስተዋል፡፡ ለጥያቄዎቹም ከድርጅቱ ጽ/በት ማብራሪያዎች
ተሰጥተዋለ፡፡
በተጨማሪም የኔፕ ፕላስ የ 5 አመት ስትራቴጂክ እቅድም ተገምግሞ መጠናቀቁን
እና ሴቶችና ሴቶች ጥምረትን ለማገዝ በጽ/ቤቱ በኩል ጥረት እየተደረገ መሆኑንም
ተብራርቷል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ጠቅላላ ጉባዔው የ2022 እቅድን ያደመጠ ሲሆን አባላቱም ግሎባል ፈንድ
ፈጻሚ ያልሆኑ አባላት ጉዳይ በእቅዱ ቢካተት፤ በጦርነት የተጎዱ ማህበራትና ሴቶች በተለየ
መልኩ የሚደገፉበት መንገድ ቢመቻች በማለት አሳስበዋል፡፡ጠቅላላ ጉባዔው ሪፖረቱንና
እቅዱን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡በመጨረሻም ጠቅላላ ጉባዔው የ2021 የውጭ ኦዲት
ሪፖረተን ካደመጠ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

NEP+ Provided Refresher training for Case managers and adherence Supporters

(February 26 2022 Pr and Communication Department)

NEP+ Provided refresher training for 814 ( male 199 and female 615) case managers and adherence support drawn from dsellected health facilities found in SNNP, Sidama, South west , Oromia, Gambella Regions and Addis Ababa City Administration.
According to the information from NEP+ program Department, the training was focused on Mental Health Illness screening, Cervical Cancer ,prevention, key messages on viral Undetected leads to Un transmitted HIV during sexual intercourse and finally on the revised data management tools. The training was given in 6 round for 2 days each
The training was given at Adama, Jimma, Bishoftu and Butt Jira Towns within three month time from December 2021 to February, 2022.

Trainees in partial.
Trainees in partial.

Sample Text

NEP+ Board of Directors Evaluated NEP+ office Performance

NEP+ Board of Directors conducted its regular meeting at Adama Town for three days (January
14-16, and evaluated NEP+ performance of 3rd quarter (July 1 to September 31, 2021) 2021.

Ato Bayia Chala, NEP+ acting executive director on his part, elaborated all the challenges the organization faced during the quarter. Ato Bayisa mentioned that shortage of budget was very crucial even to conduct board regular meeting.

The board of directors finally has conducted wide discussion on the report and advised the organization to continue its effort to mobilize additional resources. The board also advised the organization to strengthen its effort of implement capacity. The board has also discussed and passed decisions on different issues that may help the smooth operation of the Organization.

Board Meeting

According to Ato Belay, over 30 thousands of beneficiaries on ART has benefited from CDC and L Initiative projects that are currently at hand.

NEP+ Board of Directors Evaluated NEP+ office Performance

Adama, January 17, 2021 (NEP+ PR and Communication Department)

NEP+ Board of Directors conducted its regular meeting at Adama Town for three days (January 14-16, and evaluated NEP+ performance of 3rd quarter (July 1 to September 31 2021) 2021. The activity report of the organization was presented to the board by Ato Belay Reta, NEP+ M and E manager.

According to Ato Belay, over 30 thousands of beneficiaries on ART has benefited from CDC and L Initiative projects that are currently at hand.
Ato Belay in his presentation mentioned that in addition to performance of many activities, NEP+ has made great effort to mobilize additional resources for the organization. Accordingly, says Ato Belay, the NEP+ has produced over 6 projects that costs over 9 million USD and submitted different donors. He also added that the shortage of budget was bottle neck for the organization to achieve its objectives properly. Ato Belay added that the delay of global fund project and budget cut from CDC has highly affected the implementation of the activities of the organization.

Ato Bayia Chala, NEP+ acting executive director on his part, elaborated all the challenges the organization faced during the quarter. Ato Bayisa mentioned that shortage of budget was very crucial even to conduct board regular meeting.

Ato Bayisa Chala (NEP+ A/ED)

The board of directors finally has conducted wide discussion on the report and advised the organization to continue its effort to mobilize additional resources. The board also advised the organization to strengthen its effort of implement capacity. The board has also discussed and passed decisions on different issues that may help the smooth operation of the Organization. NEP+ Board members are representatives of 9 regional states and 2 City Administrations.

የኔፕ ፕላስ ቦርደ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

የኔፕ ፕላስ ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን ከጥር 6-8 2013 በአዳማ ከተማ ያካሄደ ሲሆን በስብሰባው በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የተለያዩ ውሳኔዎCን አሰተላልፈዋል፡፡ በዚው መሠረት ቦርድ ከሀምሌ 1 2913 እስከ መስከረም 30 2013 ድርስ የተከናወኑ መደበኛ ሥራዎች በድርጅቱ የክትትልና ምዘና መምሪያ ሓላፊ በሆኑት በአቶ በላይ ረታ ቀርቦል፡፡ አቶ በላይ ረታም በርፖርታቸውየግሎባል ፈንድ ሰኔ 30 2013 መጠናቀቁን አብራርተው በሩብ አመቱ ሥራዎች በዋናነት የተከናወኑት በሲዲሲ ፕሮጀክትና ከፈረንሳይ መንግስት በL IUntiative  በኩል ብቻ በተገኘ በጀት ነው ብለዋል፡፡

በፕሮጀክቶቹም ከ30 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የጸረ ኤች አይቪ መድሓኒት ተጠቃሚዎች በህክምና ቁርኝት ዙሪያ የምከክር አገልግሎት መሰጠቱን አብራረተዋል፡፡  ከዚህም በተጨማሪ የድርጅቱን አቅም ለማሰደግና የግሎባል ፈንድ እንÇ=ቀጥል ለማድርግ ከ 9 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የሚያወጡ የፕሮጀክት ሀሳቦች ተነድፈው ለሚመለከተው ድርጅቶች መሰጠታቸው ተብራረተዋል፡፡ አቶ በላይ በሩብ አመቱ የተለያዩ ድፓርትሜንቶች ተባብሮ መሥራት  ለሥራችን አቅም ነበረ ብለዋል፡፡

በሩብ አመቱ ያጋጠሙትን ችግሮች በተመለከተም በግሎባል ፈንድ በጀት መቆም፤ ቀጣዩም ቶሎ ባለመወሰኑና በሲዲሲ ከኔፕ ፕላስ ለመውጣት መዘጋጀት ምክኒያት የሰራተኛው አለመረጋጋትና በብዛት ድርጅቱን መልቀቅ ª’ኛው ችግር ነበረ ተብለዋል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ምክኒያት የኔፕፕላስ ቦርድ ከጽ/ቤቱ ጋር የነበረው መስተጋብር እየተራራቀ መምጣትም ሌላኛው ድርጅቱን የገጠመ¨< ጉል ህ ችግር ነው ተብለዋል፡፡

አቶ ባይሳ ጫላ የድርጅቱ ተ/ዳይሬክተርም ከቦርዱ የቀረቡ ጥያቄዎችና ድርጅቱን የገጠሙ ችግሮች ዙሪያ ሰፋ ያለ ማበራረያ ሰጥዋል፡፡ ቦርዱ እንደተለመደው ከድርጅቱ ጎን በሚችለው ሁሉ እንÇ=ቆምም አደራ ብለዋል፡፡
ቦርዱም በርፖርቱ ላይ ሰፊ ውይይት ካካሄደ መጨመር የሚገባቸውን ጉዳዮች በመጨመር ቦኃላ ርፖረቱን አጽድቋል፡፡

About NEP

The NEP+, formerly known as AELWHA (Association of Ethiopians Living with HIV/AIDS), is established in October 2004 to raise and relay the collective voice of people living with HIV.

GPS Location of NEP+ Office

Contact Us

Address: Mexico Chamber of Commerce building 5th floor.
Phone: +251 111 659 1414/1818/1919
Fax: +251 111 659 1010
P.O.Box: 780 Code-1250
Email: eshetu@nepplus.org / aelwha@ethionet.et