Director NEP

ኔፕ ፕላስ 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት አካሄደ

ኔፕ ፕላስ 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት አካሄደ ኔትወርክ ኦፍ ኔትወርክስ ኦፍ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕ ፕላስ) 16ኛ መደበኛ
ጠቅላላ ጉባኤውን በባህርዳር ከተማ ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታሪኩ በላቸው ሲሆኑ በንግግራቸው ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኤች.አይ.ቪ/ ኤድስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሶስት 90ዎች ፕሮግራም ወደ ሶስት 95ቶች መለወጡን አስታውሰው በተለይ በአሁኑ ሰኣት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያውን 95 ለማሳካት ሰፊ እንቅስቃሴ በተጀመረበት ወቅት ይህ ታላቅ ጉባኤ መካሄዱ ለፕሮግራሙ መሳካት ሰፊ አበርክቶ እንደሚኖረው እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
አቶ ታሪኩ በላቸው የአማራ ክልል ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ታሪኩ አያይዘውም ዓለምን እየፈተነ ያለው የኮቪድ 19 ወረርሽን ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን
ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚደረገውን ዘመቻ አስቸጋሪ እንዲሆን እያደረገው ካሉ በኋላ በኢኮኖሚ ጠንካራ ያልሆኑና አንስተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ሴቶች እህቶቻችን የኮሮና ወረርሽኝ ኑሯቸውን እጅግ አስቸጋሪ አድርጎባቸዋል፡፡

በተለይ ይህ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የኤች.አይ.ቪ ስርጭት እንዲጨምር በማድረግ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ እንዳለም የሚያመለክቱ መረጃዎች እንዳሉ የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ምክትል ቢሮ ኃላፊው በንግግራቸው መጨረሻም ጉባኤው በእቅዶቻቸው ላይ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የመከላከል ስራን እንዲካትቱ ጥሪ አድርገው የአማራ ክልል መንግስት ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን በመከላከል ረገድ ለሚደረጉ ጥረቶች አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ ድጋፍ ለመስጠት ከክልሉም ሆነ ከብሄራዊ ጥምረቱ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ ንግግራቸውን አገባደዋል፡፡ ከመክፈቻው ንግግር ቀደም ብሎ የኔፕ ፕላስ ዋና ስራ አስኪጅ ለተሰብሳቢዎቹ ባሰሙት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ኔፕ ፕላ ባለፈው የፈረንጆቹ አመት በርካታ ስኬታማ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡ በንግግራቸውም ኔፕ ፕላስ ከሲዲሲ እና ከግሎባል ፈንድ ውጪ ከሌሎች ለጋሽ ድርጅቶች የገንዘብና የአይነት እንደዚሁም የቴክኒክ ድጋፎች ማገነቱን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ በተለይ ለደርጅቱ ችግር ሆኖ የመጣው መላው አለምን ፈታኝ የሆነው የኮቪድ 19 ክስተት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

አቶ መኮንን አለሙ የኔፕ ፕላስ ዋና ዳይሬክተር ለጉባኤተኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ሲያደርጉ ይህንኑ ወረርሽኝ ለመከላከልም ኔፕ ፕላስ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝና ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችሉ የእጅ ማጽጃና የፊት መሸፈኛ ማስኮችን በድጋፍ መልክ ማግኙቱን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የድርጅቱ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ እድላም ገ/ስላሴ በበኩላቸው ቦርዱ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መደበኛ እና አስቸኳይ ስብሰባዎችን በማካሄድ የኔፕ ፕላስ የስራ ግምገማ በማድረግ በታዩ ክፍተቶች ላይ የማስተካከያ አቅጣጫዎችና የቅርብ ድጋፍ ሲያደርግለት መቆየቱን አስታውሰው ከዚህ ውጭ በአንዳንድ የክልል ጥምረቶች ላይ በታዩ ችግሮች ላይ በቦታው ድረስ በመገኘት የመፍትሄ ሀሳቦችን ተሰጥተዋል ብለዋል፡፡ አቶ እድላም ገ/ሥላሴ የኔፕ ፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት በሶስት ቀናት ቆይታቸው የድርጅቱን የቦርድ ሪፖርትና እቅድ፣ የጽቤቱን ሪፖርትና እቅድ፣ የኦዲት ሪፖርት እና አዲሱን የመተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል፡፡

የዩኤን ኤድስ ካንትሪ ዳይሬክተር ኔፕፕላስን ጎበኙ

በኢትዮጵያ የዩኤን ኤድስ ካንትሪ ዳይሬክተር እና ተወካይ ዶ/ር ፍራንሲዮስ ንዳይሺሚዬ በኔፕ ፕላስ ቢሮ በመገኘት ከስራ
አስኪያጁ እና የስራ ክፍል ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ፡፡ ካንትሪ ዳይሬክተሯ ማክሰኞ ግንቦት 2/2015 በኔፕፕላስ ቢሮ ባደረጉት
ጉብኝት የኔፕ ፕላስን ስትራቴጂክ ፕላን በመከለስ ዙሪያ፤ የኔፕፕላስን 20ኛ አመት አከባበር በተመለከተ እንዲሁም
ለኔፕፕላስ ሰራተኞችን መቅጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡
የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኔፕፕላስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ታደሰ ሲሆኑ፤ ዩኤን ኤድስ የኢትዮጵያ ተጠሪ እና
በአለም አቀፍ ደረጃ የምንሰማበት ድምጽ በመሆኑ በጣም የምንኮራበት አጋራችን ነው ብለዋል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ
የተቀመጠውን በኤች አይ ቪ ምክንያት የሚከሰት ሞትን፤ አድሎና መገለልን እንዲሁም አዲስ የኤች አይቪ የመያዝ ቁጥርን
ዜሮ የማድረስ እቅድን ለማሳካት በጋራ በመስራታችን እድለኞች ነን ብለዋል አቶ ካሳሁን፡፡ አያይዘውም ኔፕ ፕላስ
የተቋቋመለትን አላማ ከግብ ለማድረስ በተለያየ መልኩ ራሱን እያሻሻለ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥም
የድርጅቱን እስትራቴጅክ ዕቅድ ለመከለስ መዘጋጀቱ ተጠቃሽ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡፡ ኔፕ ፕላስ ብሄራዊ ስትራቴጂክ ዕቅዱ
በሚከለስበት ወቅትም ኔፕ ፕላስ ተሳትፎ ማድረጉንም አቶ ካሳሁን ጨምረው ገልዋል፡፡

ዶ/ር ፍራንሲዮስ እና አቶ እሸት ደገፋ ከአቶ ካሳሁን ታደሰ ጋር ውይይት ሲያደርጉ
ዶ/ር ፍራንሲዮስ፤ ዩ ኤን ኤድስ እንደ ድርጅት ኔፕ ፕላስን እንደ ቤቱ ነው የሚቆጥረው ያሉ ሲሆን፤ የቫይረሱን ስርጭት
ለመግታት በሚደረገው ርብርብ ላይ በጋራ ለመስራት ሙሉ ዝግጁነታቸውን አብራርተዋል፡፡ ድርጅታቸው ምንም እንኳን
በገንዘብ ድጋፍ ማያደርግ ድርጅት ቢሆንም፤ ኔፕ ፕላስ ገንዘብ ሊያገኝ በሚችልበት ሁኔታ ላይ እና በቴክኒክ ለማገዝ
ፈቃደኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ከኔፕ ፕላስ የሚጠበቀውም ጥሩ ፕሮፖዛሎችን ማዘጋጀት እና የሚገኘውን ገንዘብም
በአግባቡ ፤ ግልጽነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት እንዲሁም ሃላፊነት በተሞላበት መንገድ መጠቀም እንደሆነም አስረግጠው
ተናግረዋል፡፡ ቫይረሱ በደማቸው ያለ ወገኖች የተሻለ እና የተስተካከለ ህይወት መምራት እና የሚያስፈልጓቸውን
አገልግሎቶችም ያለ ምንም ችግር ማግኘት ይገባቸዋል ያሉት ዶ/ር ፍራንሲዮስ፤ በአሁኑ ወቅት ህክምናው በነጻ በመሰጠት
ላይ በመሆኑ አንድም ሰው በኤች አይ ቪ ምክንያት መሞት እንደሌለበትም ተናግረዋል፡፡ ኔፕፕላስም ሆነ ዩ ኤን ኤድስ ዋና
ተግባራቸው ሊሆን የሚገባው ከኤች አ ይ ቪ ጋር ተያይዞ የሚፈጠር አድሎና መገለልን ማስወገድ እንደሆነም ዳይሬክተሯ
ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ግጭቶች ባሉባቸው አካባቢዎች ሰብኣዊ ቀውስ አለ ሲባል በሁሉም አእምሮ ውስጥ የሚመጣው ስለሌሎች
በሽታዎች እንጂ ስለ ኤች አይ ቪ እንዳልሆነ ፤ ነገር ግን ቫይረሱ ያለባቸው ወገኖች ከየትኛውም ህብረተሰብ ክፍል የበለጠ
እየተጎዱ እንደሆነም ዳይሬክተሯ ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ማህበራትም ሆኑ ኔትዎርኮች ከኤች አይ ቪ የጸዳ
ትውልድ እንዲፈጠር እና አድሎና መገለልም እንዲቀንስ ስለጉዳዩ ደጋግመው መነጋገር እና በርትተው መስራት
እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡ በሃገሪቱ በሚገኙ የተወሰኑ አካባቢዎች ያሉ ማህበራትን የመጎብኘት እድሉ እንደነበራቸው
የገለጹት ካንትሪ ዳይሬክተሯ፤ ኤች አይ ቪን በከመቆጣጠር እና ስርጭቱን በመከላከል ስራ ውስጥ የማህበራት መኖር
ወሳኝ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ከማህበረሰቡ ጋር መስራት ካልተቻለ ኤች አይ ቪን የመከላከል ስራው
ውጤታማ እንደማይሆንም አስረድተዋል፡፡
ለኤች አይ ቪ እና ተያያዥ ጉዳዮች ብዙም ትኩረት ባለመሰጠቱ ጉዳይ ላይ የተስማሙት አቶ ካሳሁን፤ ደርጅቱን ስትራቴጂክ
ዕቅድ መከለስ ያስፈለገውም ከዚህ ጋር በተያያዘ መልኩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኤ ች አይ ቪን ጉዳይ እንደ አዲስ ማንቀሳቀስ
እና ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚያስፈልግም ተጠቅሷል፡፡ ይሄንን ለማድረግም የድርጅቱ
20ኛ አመት አከባበር ወሳኝ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ክብረ በአሉ የድርጅቱን እንቅስቃሴዎች ለመላው አለም ለማስተዋወቅ
እና ቫይረሱ ያለባቸውን ወገኖች ድምጽ ለማሰማት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆንም አስረድተዋል፡፡ በዩኤን ኤድስ
የEquality for all officer አቶ እሸት ደገፋ በበኩላቸው፤ ኔፕፕላስ በሚሰራቸው ስራዎች በርካቶችን መድረስ የቻለ እና
የብዙዎችን ህይወት መለወጥ የቻለ ተቋም በመሆኑ በቀጣይም አብሮ ለመስራት ሙሉ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል፡፡ እንደ
ባለሞያም ኔፕ ፕላስ እገዛ በሚያስፈልገው ጊዜ ሁሉ ለማገዝ ፈቃደኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
የኔፕ ፕላስ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሃላፊ አቶ ጌታቸው ጎንፋ በበኩላቸው ዩ ኤን ኤድስ እና ኔፕ ፕላስ የኤች አይ ቪን
ስርጭት ለመቀነስ በሚሰሩ ስራዎች ረገድ ለረጅም ጊዜ በጋራ በርካታ ስራዎችን ሲሰሩ እንደነበረ በማስታወስ፤ በቀጣይም
የተሻሉ በርካታ ስራዎችን ለመስራት እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ዩ ኤን ኤድስ በቴክኒክም ሆነ በተለያዩ መንገዶች ኔፕ
ፕላስን መደገፉ የቫይረሱን ስርጭት በመግታት እንቅስቀሴው ላይ ጉልህ ሚናን እንደተጫወተም አቶ ጌታቸው ጨምረው
ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ፍራንሲዮስ እና አቶ እሸት ደገፋ ከኔፕፕላስ ማናጅመንት አባላት ጋር ውይይት ሲያደርጉ
የኔፕ ፕላስ ክትትልና ምዘና ክፍል ሃላፊ አቶ በላይ ረታ ደግሞ ዩ ኤን ኤድስ በኔፕ ፕላስ እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛውን
ሚና እንደተጫወተ በመጠቆም፤ ምስጋናቸውንም አቅርበዋል፡፡ ለአብነት ያህልም ኔፕ ፕላስ የግሎባል ፈንድን ግራንት
እንዲያሸንፍ ዩ ኤን ኤድስ ከፍተኛውን እገዛ እንዳደረገ በማስታወስ በቀጣይም የበለጠ አብሮ ለመስራት ዩ ኤን ኤድስ
ዝግጁ በመሆኑ ገልጸዋል፡፡

እንግዶቹ ከኔፕፕላስ ዳይሬክተር እና ከፊል ሰራተኞች ጋር
ስትራቴጂክ ዕቅድ መከለስን በተመለከተ ዩ ኤን ኤድስ የ2024/25 እቅድን በመስራት ላይ በመሆኑ በዚሁ አግባብ
እንደሚታይ ዶ/ር ፍራንሲዮስ በውይይት መድረኩ ላይ አብራርተዋል፡፡ የኤች አ ይ ቪን ጉዳይ እንደ አዲስ ማነቃቂያ
መፍጠርም ሆነ ተሰሚነትን ማምጣት እና ግንዘቤ መፍጠር ገንዘብ የሚጠይቁ ባለመሆናቸው አጠናክሮ መስራት
እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡ ኔፕ ፕላስ ከሌሎች ድርጅቶች የተለየ መሆኑን እና የቫረሱን ስርጭት በመግታቱ ረገድ
ያለውን የጎላ ሚና ማሳየት እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ይሄንንም የ20ኛ አመት ክብረ በአሉን በሚያከብርበት ወቅት
ተጨባች ስራዎችን በማቅረብ ምን ያህል ለውጥ ፈጣሪ መኑን ማሳየት አለበት ሲሉ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ዶ/ር ፍራንሲዮስ ዩ ኤን ኤድስ በአጠቃላይ ኔፕ ፕላስ ኤች አይ ቪን ለመከላከል በሚያደርጋቸው እንቅስቃዎች ሁሉ ከጎኑ
መሆኑን የገለጹ ሲሆን ፤ ለድርጅቱ ሰራተኛ መቅጠር ከፍተኛ ወጪ እና ሃላፊነት የሚጠይቅ በመሆኑ አሁን ላይ ይሄን
ለማድረግ ቃል መግባት እንደማይቸሉ ገልጸው፤ ነገር ግን ሃብት በማፈላለግ ስራው ላይ በሙሉ ፈቃደኝነት
እንደሚሳተፉ አስረድተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ በተለይ በትግራይ ክልል ከፍተኛ የኮንዶም እጥረት መኖሩን በመጥቀስ
ዩ ኤን ኤድስ ምን አስቧል ተብለው የተጠየቁት ዶ/ር ፍራንሲዮስ፤ አሁን ላይ ኮንዶምን በተመለከተ ያለው ችግር የገንዘብ
ሳይሆን የጥራት ጉዳይ ነው ያሉ ሲሆን፤ ጉዳዩ በሌላ አካል የሚታይ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ካንትሪ ዳይሬክተሯ በቀጣይም
ከኔፕ ፕላስ ጋር መሰል ውይይቶችን በየ ሁለት ወሩ ለማድረግም ስምምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

የግሎባል ፈንድ (New Funding Model 3) በአግባቡ አየተፈጸመ መሆኑ ተገለጸ

በኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎረክስ ኦፍ ኤች አይቪ ፖሲቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕ ፕላስ) እየተተገበረ ያለውና
በጸረኤች አይቪ ህክምናና ቁርኝት ላይ ያተኮረው ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
ይህ የተገለጸው በአዳማ ከተማ ናፍሌት ሆቴል ከነሓሴ 3 አስከ 6 2015 ዓ.ም በተካሄደው የዕቅድ
ክለሳ አውደ ጥናት ላይ ሲሆን፤ በአውደ ጥናቱም ላይ የየክልሉ የቦርድ ተወካዮች፤ ዳይሬክተሮች፤
የፕሮግራም ኃላፊዎች ከ12ቱም ጥምረቶች የተወጣጡ ከ67 በላይ የሚሆኑ ባለሙያዎች ተሳታፊ
ዎች እንዱሁም የጤና ሚኒስቴር ተወካዮችም እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡


የዕቅዱ ተሳታፊዎች በከፊል
በዚህ በአቶ ካሳሁን ታደሰ የድርጅቱ ዳይሬክተር የእንኳን ደህና መጣችወሁ ንግግር በተከፈተው አና
በድርጅቱ የቦርድ ፕሬዝዳንት በአቶ አብዱራሂማን ከማል መልዕክት በተዘጋው ስብሰባ ላይ
እንደተብራራው ባለፉት 1 ዓመት ከ6 ወራት ብቻ በቤት ለቤት እንክብካቤ አገልግሎት 131 ሺህ 734
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝባቸው ወገኖች ህክምናቸውን እንዳያቋርጡ የምክክር አገልግሎት
አግኝተዋል፡፡ በሪፖርቱ ከ,14 ሺህ725 በላይ የሚሆኑት ከህክምናቸው ጠፍተው የነበሩ ታካሚዎች
ደግሞ አስፈላጊው ፍለጋና የምክክር አገልግሎት ተሰጥቷቸው ወደ ህክምናቸው እንዲመለሱ
እንደተደረጉ ተግልጿል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ከ 28 ሺህ 499 በላይ የሚሆኑና የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸው ታካሚዎች ለተለያዩ
ድጋፎች ወደ ተለያዩ ድርጅቶች ተልከው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ እንደተደረገ ከቀረቡት
ሪፖርቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡ አድሎና ማግለልን ለመቀነስም ከ33 ሺህ 555 በላይ የህብረተሰብ
ክፍሎች የግንዛቤ ማዳበሪያ ትምህርት ተሰጥቶቿል ተብሏል፡፡

ተሳታፊዎች በከፊል
በአፈጻጻሙ ወቅት የገጠሟቸውን ችግሮች እያንዳንዱ ክልል ተራ በተራ ያቀረቡ ሲሆን፤ የፍላጎትና
አቅርቦት አለመጣጣም፤ የዕቅዱ ከላይ ተዘጋጅቶ መውረድና በአፈጻጻሙ ላይ ግልጽ አቅጣጫ
አለመቀመጥ፤ የሪፖርት ቅጾች ግልጽነት መጓደልና የመሳሠሉት ናቸው ተብሏል፡፡ በተነሱት ችግሮች
ዙሪያም ማብራሪያዎች የተሰጡ ሲሆን፤ በመቀጠልም የሚቀጥለው የ2016 የአንድ አመት ዕቅድ
ቡድን በቡድን በመከፋፈል ከልሷል፡፡
ኔፕ ፕላስ እስከ ፕሮጀክቱ መጨረሻ ድረስ 300 ሺህ ለሚሆኑት ተጠቃሚዎች የጸረኤችአይቪ
ህክምናቸውን እንዳያቋርጡ ለመደገፍ የ7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የ3 ዓመት ፕሮጀክት ከጤና
ሚንስቴር ጋር መፈራረሙ ይታወሳል፡፡

ኔፕፕላስ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ

ኔትወርክ ኦፍ ኔትወርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን
ግንቦት 3 እና 4 ቀን 2015 ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ሊሳክ ሆቴል አካሄደ፡፡ በጉባዔው ላይም የድርጅቱ የቦርድ አባላት፡
የጠቅላላ ጉባዔ አባላት፣ የኔፕፕላስ ሰራተኞች እና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል፡፡
በጠቅላላ ጉባዔው ላይ በርካታ መልዕክቶች፣ የየስራ ክፍሉ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቶች እንዲሁም የ2023 አመታዊ
እቅድ የቀረቡ ሲሆን ከጉባዔው ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶች እንዲሁም ጥቆማዎች የተሰነዘሩ
ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎች ማብራሪያ በሚመለከተው አካላት ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በጉባኤው ላይ በመጀመሪያ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኔፕፕላስ እክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ
ካሳሁን ታደሰ ሲሆኑ፣ እርሳቸውም በንግግራቸው ድርጅቱ ከ20 አመታት በላይ ለችግር የተዳረጉ ወገኖችን
ከወደቁበት ችግር እያነሳ የቆየ ድርጅት ቢሆንም አሁን ግን በተለያዩ ምክንያቶች ከፍተኛ አደጋ የተጋረጠበት
በመሄዱ ቀድሞ አብረው ይሰሩ የነበሩ አጋሮቻቸን ወደ ኋላ እያፈገፈጉ ነው ብለዋል፡፡ አቶ ካሳሁን ድርጅቱን አሁን
ካለበት ደረጃ ከፍ ለማድረግ ከፍተኛ ሃላፊነት እንደተሰጣቸው በመጠቆም፤ ደርጅቱን ወደ ቀድሞ አቋሙ
ለመመለስ ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዞ አና ተስማመቶ በየደረጃው ያለበትን ሃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባም
አሳስበዋል፡፡

አቶ ካ ሳ ሁ ን ታደሰ የኔፕ ፕላስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር
በማስከተል በፌደራል ጤና ሚኒስቴር ኤች አይ ቪ መከላከል እና መቆጣጠር ጽ/ቤት የዘርፈ ብዙ ምላሽ ዴስክ
ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ካሳ ከማንኛውም ጊዜ በላይ አንድ ሆነን ጥምረቱን መደገፍ አለብን ያሉ ሲሆን፤ ድርጅቱ
ለተቋቋመለት አላማ መኖሩን እየዘነጋ የመጣ ስለሆነ መንቃት ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡
ኔፕ ፕላስ ለጤና ሚኒስቴር የውጭ አካል ሳይሆን እንደ ራሳችን አንዱ ክፍል አድርገን የምቆጥረው ስለሆነ
ድክመቱን ማየት አያስደስተንም ብለዋል አቶ ሀብታሙ፡፡ ሶስቱን 95 በማሰካት ረገድ የኔፕ ፕላስ ሚና ከፍተኛ
እንደሆነ የገለጹት አቶ ሀብታሙ፤ አሁንም የቫይረሱን ስርጭት ወደ 0.3 በመቶ ለማውረድ እየተጫወተ ያለው
ሚናም ቀላል የሚባል ባለመሆኑ፤ የጤና ሚንስቴር አንዱ አካል ነው የምንለው በምክንያት ነው ብለዋል ኃላፊው፡፡
በአገራችን ብዙ ድርጅቶች ቢኖሩም ኔፕ ፕላስን የሚተካ ሊኖር አይችልም ያሉት አቶ ሀብታሙ፤ ጥምረቱ ከሌሎች
አጋር ድርጅቶች ጋር ቁርኝቱን የበለጠ አጠናክሮ ለመስራት ራሱን በከፍተኛ ደረጃ ምቹ ማድረግ እንዳለበትም
አሳስበዋል፡፡ ያሉትን የጤና ፖሊሲዎች መሬት ለማስያዝ እና ተግባራዊ ለማድረግ የኔፕ ፕላስም አስተዋጽኦ
ከፍተኛ እንደሆነ ነው አቶ ሃብታሙ የገለጹት፡፡ ሚኒስትሩ ወደፊትም ኔፕ ፕላስን በሁሉም መንገድ ለመደገፍ እና
ተጠያቂነትን ለማስፈን የጂፓ ፕሪንሲፕልን ለመተግበርም ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ በድርጅቱ በኩል ግን
ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ በሰፊው አቅዶ መንቀሳቀስ ያለበት ተጽእኖ ፈጣሪ ድርጅት
ሆኖ መታየት ባለበት ሁኔታ ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ ሃብታሙ፤ ይሔን ማድረግ ከቻለ ከመንግሰት በጀት
ማስለቀቅም ሆነ ሌሎች ለጋሽ አካላትን ለመሳብ ቀላል ይሆንለታል፡ በማለት ሀሳባቸውን ቋጭተዋል፡፡

አቶ ሃብታሙ ካሳ በፌደራል ጤና ሚኒስቴር ኤች አይ ቪ መከላከል እና መቆጣጠር ጽ/ቤት የዘርፈ ብዙ ምላሽ ዴስክ ኃላፊ
በመቀጠል የኔፕፕላስ የበጀት አመቱ የስራ ክንውን ሪፖርት በድርጅቱ ክትትልና ምዘና መምሪያ ሃላፊው አቶ
በላይ ረታ የቀረበ ሲሆን፤ በሪፖርቱ የቀረቡት ዋናዋና ነጥቦችም የሚከተሉት ናቸው፡፡ እንደ ማኔጅመንት ከፍተኛ
ትኩረት ተሰጥቶ ከተሰራባቸው ስራዎች ዋና ዋናዎቹ የግሎባል ፈንድ ፕሮጀክት እና የፈረንሳይ ፕሮጀክቶችን
ለማስቀጠል ፤የሲዲሲ ፕሮጀክት ቁሳቁሶችና ተሸከርካሪዎች እንዳይወሰዱ፤ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወጣቶች
ማህበር (አስክ አስ) እንዲመሰረትና እንዲጠናከር ጥረት ማድረግ ተጠቃሽ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ የፍራንስ
ኢኒሸቲቭ ፕሮጀክት ከፈረንሳይና ከአገር ውጪ በመጡ ኦዲተሮች ኦዲት እንዲያደርጉ ተደርጓል ብሏል፡፡
በተጨማሪም በኤል ኢኒሸቲቭ በጀት ለአቻለአቻ አስተማሪዎችና ፕሮጀክት ኦፊሰሮች፤ ለአማካሪዎች እና በግሎባል
ፈንድም የአሰልጣኝ ስልጠና መሰጠቱን፤የጥምረቶችና የማህበራት መሪዎችም የአመራር ክህሎት ስልጠና
እነደተሰጠ አብራረተዋል አቶ በላይ በርፖርታቸው፡፡ ወርክ ሾፕን በተመለከተም በተለይ አድሎና ማገለልን
ለመቀነስ ከተለያዩ የፓላማ አባላት እና የሲቪል ሰርቪስ አባላት፤ከክልሎች እና የጉዳዩ ባለቤት ከሆኑ አካላት ጋር
በርካታ ስብሰባዎች ተካሂደዋል ተብሏል በሪፖርቱ፡፡ በድጋፍና እንክብካቤ ደግሞ 12,363 ከህክምና ቀጠሯቸው
የጠፉ ደንበኞች ፍለጋ ተደርጎላቸው ወደ ህክምና አገልግሎት የተመለሱ ሲሆን፤ 8,058 ድጋፍና ክብካቤ
የሚያስፈልጋቸው ደንበኞችንም ወደ ድጋፍ ሰጭ አካላት ተልከው ድጋፍና ክብካቤ እንዲያገኙ ተደርጓል በአቶ
በላይ ገለጸ መሠረት፡፡ ህክምና የሚያስፈልጋቸው 2,719 ሰዎች ደግሞ ወደ ተለያዩ ጤና ተቋማት በመላክ ህክምና
እንዲያገኙ መደረጉም በዚው ርፖርት ተብራረቷል፡፡

አቶ አብ ዱርሃማ ን ከማ ል የኔፕፕላስ ቦርድ ሰብ ሳቢ
ከህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ጋር በተያያዘም 3ቱን 95 ለማሳካት እንዲረዳ በሶስት ቋንቋዎች የአን አንደ ደቂቃ
የቲቪ እና የሬዲዮ መልክቶች ተዘጋጅተው መሰራጨታቸውን፡ በዩዩ ላይ ያተኮረ 8000 ብሮሸሮች ታትመው
መሰራጨታቸውን፤ የአድሎና ማግለል የመቀነሻ ስተራቴጂ መዘጋጀቱን፤ የአድሎና ማግለል የጥናት ውጤትም
1000 ኮፒ ታትሞ መሠራጨቱን አቶ በላይ በርፖርታቸው አብራርተዋል፡፡


ተ ሰብ ሳቢዎ ች በ ከ ፊል
የኔፕፕላስ ስራ አመራር በበኩሉ የበጀት አመቱን ክንውን ያቀረበ ሲሆን በዋናነት ለድርጅቱ አዲስ ስራ አስኪያጅ
የመሾም፤ የውጭ ኦዲተሮችን ቅጥር መከናወኑ፤ ሃብት የማሰባሰብ እንዲሁም ስብሰባዎችን ማካሄድ ዋናዋና
እቅዶቹ የነበሩ ሲሆን ከእነዚህ እቅዶች መካከል ያሳኩአቸውን የቦርድ ሰብሳቢው አቶ አብዱርሃማን ከማል
በዝርዝር አቅረበዋል፡፡ ታቅደው ያልተሳኩትንም በቀጣይ ለማሳካት በእቅዳቸው ውስጥ ማካተታቸው በዚው ጊዜ
ተገልጿል፡፡ በመቀጠልም የ2023 አመታዊ እቅድ የቀረበ ሲሆን፤ በዚህ በጀት አመት ከተያዙ እቅዶች መካከልም
ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው የኔፕፕላስን ገጽታ እና መልካም ስም የመገንባት ሥራ፤ በቂ ሃብት ማበልጸግ
አንዲሁም ወጥነት ያለውና የተስተካከለ የፋይናነስ አስተዳደር ማስፈን ናቸው፡፡
በዋና ዳይርክተር ልዪ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊሰሩ ከታቀዱ ስራዎች መካከል ቫይረሱ በደማቸው ያለ ወገኖች
በተለያዩ መድረኮች እና ፕሮግራሞች ላይ በመሳተፍ ለሌሎች ወገኖች ድምጽ እንዲሆኑ ጠቃሚ ልመዶችንና
የሃብት ማግኛ እድሎች መፍጠር፤ መረጃዎችን፣ መልእክቶችና ውሳኔዎችን ማስተለላፍ፤ በተቋሙ ስር ያሉ አባል
ደርጅቶችናየስራ ክፍሎች የድርጅቱን አላማ ሊያሳካ በሚያስችል መልኩ ሃብት እንዲያፈላልጉ፤ አሳታፊ በሆነ
መልኩ እንዲያቅዱ እና እንዲተገብሩ እገዛ እና ክትትል ማድረግ፤ ስራዎች ውጤት ተኮር እንዲሆኑ መደገፍ እና
አዳዲስ ተግባራትን ማከናወን ብሄራዊ ጥምረቱን፣ የአባል ጥምረቶችን እና ማህበራትን ተቀባይነት እና
ተወዳዳሪነት ማሳደግ ከመንግስት አካላት፤ ከለጋሽ ድርጅቶች፣ ከባለድርሻ አካለት ፣ ከማህበረሰቡ እና
ከሚዲያዎች ጋር ቀጣይነት ያለው መልካም ግንኘነት በመፍጠር የድርጅቱን ገጽታና የገቢ ምንጭ ማሳደግ፤
ድርጅቱን በአጠቃላይ ብቁ ተወዳዳሪና ተወዳጅ ማድረግ ዋናዋናዎቹ ናቸው፡፡በሌላ በኩል ደግሞ በፕሮግራም
የስራ ክፍል የታቀዱ እቅዶችም ቀርበዋል፡፡

የጠ ቅላላ ጉባዔ መሪዎች
ከእነዚህ ተግባራት መካከልም ለ47 ፒር ኢዱኬተሮችና ለ 8 ኦፊሰሮች እንዲሁም ለ 30 አማካሪዎች፣ ለ31
ወጣቶች የተለያዩ ስልጠናዎችን መስጠት፤ ደምበኛ ተኮር አገልግሎት የሚሰጡ 34 የጤና ባለሞያዎችን እንዲሁም
ፍላጎትን መሰረት ባደረገ መልኩ 235 የወጣቶች ቤተሰቦችን ማሰልጠን ፤ የፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ቦታዎች ላይ 4
ቫይረሱ በደማቸው ያለ ወጣት ማህበራትን እንዲመሠረቱ ማገዝ፤ በግሎባል ፈንድ 300 ኮሙኒቲ ኬዝ
ማናጀሮችንና 600 ኮሙኒቲ አድሄረንስ ሰፖርተሮችን በመጠቀም 12 ሺህ ከህክምና ክትትል የጠፉ ደንበኞችን
ፈልጎ መመለስ፤ በግሎባል ፈንድ የ3 ቀን የሪፍሬሽመንት ስልጠና ለ 300 ኮሙኒቲ ኬዝ ማናጀሮች እና ለ 600
ኮሙኒቲ አድሄረን ሰፖርተሮች ስልጠና መስጠት በዋናነት የተያዙ እቅዶች ናቸው፡፡
በጉባዔው ላይ ከቀረቡት እቅዶች ሌላኛው ደግሞ በህዝብ ግንኙነትና ኮመሙኒኬሽን መምሪያ የታቀዱ እቅዶች
ናቸው፡፡ በዚህ የስራ ክፍል ሊሰሩ ከታቀዱ ስራዎች መካከል በኤች አይ ቪ ምክንያት የሚደርሱ መድሎ
መገለሎችን ማስወገድ የሚረዱ ውይይቶችን ከሃይማኖት አባቶች ፣ የህግ አስፈጻሚዎችና መገናኛ ብዙኃን
ባለሞያች ጋር ማካሄድ፤ አስተማሪ መልእክቶችን በ5 ቋንቋዎች በክልል ኤፍ ኤም ጣቢያዎች ማስተላለፍ ፣አመታዊ
ህትመቶችን አሳትሞ ማሰራጨት እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ በመጨረሻም ጠቅላላ ጉባኤው በቀረቡት ርፖርቶችና
ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት በማካሄድ አጽድቆታል፡፡

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) የግሎባል ፈንድን አፈጻጸም ገመገመ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) የግሎባል ፈንድን አፈጻጸም
ገመገመ
ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) የሩብ አመት የግሎባል ፈንድ ፕሮግራም
ግምገማ አካሄደ፡፡ ግምገማው ከሰኔ 8 እስከ 10 ቀን፣ 2015 ዓ.ም በአዳማ ናፊሌት ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በግምገማ መርኃ ግብሩ
ላይም የኔፕፕላስ ስራ አመራር ቦርድ አባላት፤ የክልል ጥመረት ስራ አስኪያጆችና ከፍተኛ ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና
ሚኒስቴር ተወካዮች እና የኔፕፕላስ ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡
በኔፕላስ ክትትልና ምዘና መምሪያ ኃላፊ አቶ በላይ ረታ ፕሮገራሙን ካስተዋወቁ በኃላ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት
የኔፕፕላስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ታደሰ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ፕሮግራሙ ክልሎች በምን ሁኔታ ላይ
እንደሚገኙ ለመገምገም እና ለሚቀጥለው የግሎባል ፈንድ በጀት ጥያቄ ላይ ለመወያየት ፤ ልምድ ለመለዋወጥ እና የጋራ
እርምጃ ለመውሰድ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


አቶ ካሳሁን ታደሰ የኔፕ ፕላስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር
በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ም/ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ ባላቆ በበኩላቸው ኤች አይ ቪ በአሁኑ
ወቅት ድምጹን አጥፍቶ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ በመሆኑ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡ የኤ አይ ቪ ስርጭትን
ለመግታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቀዳሚውን ሚና የሚጫወተው ኔፕ ፕላስ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ጉሻ፤ በዚህ ረገድ
ድርጅቱ በሚሰራቸው ስራዎች ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ክልላቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ ላይም ሁሉም የክልል ጥምረቶች የየሩብ አመት የፕሮግራም አፈጻጸማቸውን ሪፖርት አቅርበው ሰፊ
ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ክልሎች ያቀረቧቸው ሪፖርቶች በአብዛኛው ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው ሲሆን፤ እንደ የክልሎቹ
ተጨባጭ ሁኔታም በስራቸው ላይ ገጥመዋቸው የነበሩ ተግዳሮቶችን አንስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ጥምረት ባቀረበው የሩብ አመት የፕሮግራም ሪፖርት በተጠቀሰው ጊዜ ያከናወናቸውን ስራዎች በዝርዝር
ያቀረበ ሲሆን እንደ መልካም ተሞክሮ ያነሷቸውን ነጥቦችም አስቀምጠዋል፡፡ ጥምረቱ በአብዛኛው በበጎ ፈቃደኞት የሚሰራ
እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፤ ዋና የትኩረት አቅጣጫውም ቫይረሱ ኖሮባቸው ከክትትል የጠፉ ግለሰቦችን የማፈላለግ እና2
በመድሃኒት ላይ እንዲቆዩ ማድረግ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ እነዚህን ተግባራት በሚያከናውኑበት ወቅትም በርካታ ቫይረሱ
ያባቸው ወገኖች ከግንዛቤ እጥረት የተነሳ መድሃኒታቸውን አቋርጠው ወደ ጸበል እና ገዳም መሄድ ፤ የጋራ እቅድ ሥራውን
በተመለከተ አለማቀድ ፤ ጥራት ያለው ሪፖርት በወቅቱ አለማቅረብ፤ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን አለመስጠት፤ የሰራተኞች
መቀያየር እና የጸጥታ ችግር ዋና ዋናዎቹ በአፈጻጻም ላይ ያጋጠሙ ችግሮች ናቸው ተብለዋል፡፡ እነዚህን ተግዳሮቶችም
በተለያየ መልኩ መቋቋም መቻላቻው በሪፖርቱ ወቅት ቀርቧል፡፡
ጥምረቱም የራሱ የሆኑ ምርጥ ተሞከሮ ያላቸውን ያቀረበ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከልም ከለጋሾች ከሚለቀቅላቸው ፈንድ
በተጨማሪ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ጽፈው ሃብት ማፈላለግ መቻላቸው፤ በአፍላ ወጣቶች ላይ የኤች አይ ቪ መከላከል
ስራዎችን መስራታቸው፤ ማጭበርበር እንዳይከሰት የሚያግዝ ፖሊሲ ማውጣታቸው እንዲሁም አደጋ የማስወገጃ
መንገዶችን ስራ ላይ ማዋል ናቸው ተብሎዋል፡፡


የስብሳባው ተሳታፊዎች በከፊል
ሌላው በጉባኤው ላይ የአፈጻጸም ሪፖርቱን ያቀረበው የሱማሌ ክልል ጥምረት ነው፡፡ ጥምረቱ ልክ እንደሌሎች ጥምረቶች
ሁሉ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባራት በዝርዘር ያቀረበ ሲሆን፤ በዋናነትም አድቮኬሲ ስራዎች ላይ ትረት
አድር እየሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም በዚህ በተቀመጠው ጊዜ ውስት 46 ከህክምናው ወጥተው የነበሩ ታካሚዎችን
ወደ ህክምና መመለስ መቻሉን ገልጿል፡፡ ጥምረቱ እነዚህን ስራዎች በበርካታ ውጣ ውረዶች ውስጥ ሆኖ እያከናወነ
እንደሆነ የገለጸ ሲሆን፤ በበጀት እጥረት ምክንያት ስራውን እየሰራ ያለው በአንድ ከተማ ላይ ብቻ እንደሆነም አንስቷል፡፡
በተጨማሪም ሶስት ማህበራት ቢሮ እንደሌላቸው ተገልጿል፡፡ ከቤቱ በተሰጠው ምላሽም ጥምረቱ የአድቮኬሲ ስራ የሚሰሩ
ሰዎች ራሰቸውን ግልጽ አድርገው እንዲያስተምሩ ቢደረግ መልካም ነው፤ ኔፕፕላስን ብቻ ከመጠበቅ ይልቅ ከክልሉ ጤና ቢሮ
ጋር በጋራ በመስራት የቢሮ እና የመሳሰሉ ችግሮቹን ለመቅረፍ ቢሰራ የሚል ሃሳብም ተሰጥቷል፡፡
በመቀጠል የአማራ እና የጋመቤላ ጥምረቶች የአፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡ የአማራ ጥምረትም በሪፖርቱ
ምንም እንኳን ክልሉ በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የቆየ ቢሆንም በተቻለው አቅም ቫይረሱ በደማቸው ያለ ወገኖች ተገቢውን
አገልግሎት በሚያገኙበት ሁኔታ ላይ ጥምረቱ የራሱን ጥረት ሲያደርግ እንደቆየ ገልጿል፡፡ በቀጣይም የበለጠ ስራ ለመስራት
የልምድ ልውውጥ ማድረግ ያስፈላጋል፤ በዚህም ድክመቶቻችንን ለማስወገድ እና ጥንካሬያችንን ለማስቀጠል ይረዳናል
ብለዋል፡፡ የጋመቤላ ጥምረት በበኩሉ በዋናነት ታካሚዎችን ወደ ህክምና የመመለስ ስራዎች ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን
የገለጸ ሲሆን ተጨማሪ ፋሲሊቲዎችን በመክፈት የጠፉትን ሙሉ በሙሉ መመለስ መቻሉን በሪፖርቱ አስቀምጧል፡፡3
በተጨማሪም ከግሎባል ፈንድ ድጋፍ ውጪ ጥምረቱ የራሱን ገቢ በመፍጠር እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው አካላት የምግብ
ድጋፍ እያደረገ መሆኑን እንደ ጥሩ ተሞክሮ አስቀምጧል፡፡ ሰፖርቲቭ ሱፐርቪዢን በመዳከሙ የተነሳም ዶክመንቶች
በአግባቡ ተደራጅተው የመያዝ ችግር እንዳለ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
በቀጣይነት ሪፖርቱን ያቀረበው የአዲስ አበባ ጥምረት በበኩሉ ከተማዋ የኤች አይ ቪ ስርጭት ከፍተኛ የሆነባት ከተማ
እንደመሆኗ የሚፈለገውን ያህል መስራት እንዳልተቻለ ገልጿል ፡፡ በከተማዋ ውስጥ 58 ያህል ከፍተኛ ኤች አይ ቪ ስርችት
ስጋት ያለባቸው ወረዳዎች ያሉ ቢሆንም ጥምረቱ እየሰራ ያለው ከ3ቱ ወረዳዎች ጋር ብቻ መሆኑንም እንደማስረጃ
አስቀምጧል፡፡
በከፍተኛ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የነበረችው ትግራይ ክልል ጥምረትም የአፈጻጸም ሪፖርቱን ያቀረበ ሲሆን፤ በክልሉ ላይ
በጦርነቱ ሳቢያ ብዙ ነገሮች በመውደማቸው ቫይረሱ ያለባቸው ወገኖች ደግሞ የበለጠ ተጎጂዎች ሆነዋል፡፡ በሪፖርቱ
እንደተገለጸው የቫይራል ሎደ መለኪያ፤ የመመርመሪያ መሳሪያዎች፤ የኮንዶም እና የመድሃኒት እጥረት ከመኖሩም በላይ
መድሃኒቱን ያገኙ ሰዎች እንኳን መድሃኒቱን ለመዋጥ የሚያስፈልጋቸው ምግብ እየተቸገሩ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅም ቢሆን
ሌሎች የሚወስዱትን መድሃኒት ማግኘት ስለማይቸሉ ከአመታት በፊት ይሰጥ የነበረውን ጸረ -ኤች አይ ቪ መድሃኒት
በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ እና ሌሎች ተጓዳኝ ህመሞችንም ለመታከም ችግር ላይ መሆናቸው በሪፖርቱ ተብራርቷል ፡፡
የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ካለፈ ከስድስት ወር በላይ በመሆናቸው መሳሪያዎች ጭምር በመጠቀም ላይ እንደሆኑ ሪፖርቱ
ገልጿል፡፡ ይህ ደግሞ ትክክለኛውን ውጤት ማሳየት ስለማይችል ነገሮችን የበለጠ ውስብስብ እያደረጋቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡
በርካታ ህጻናት ከቫይረሱ ጋር እየተወለዱ እንደሆነና እንዲሁም ችግሩ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ስራቸውን ለመስራት ትልቅ
እንቅፋት እንደፈጠረባቸውም ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡
የሃረሪ፤ የድሬደዋ፤ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ደቡብ ክልል ጥምረቶችም የየራሳቸውን የእፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፤
ሁሉም ክልሎች የየራሳቸውን ተግባራት በዝርዘር አቅርበዋል፡፡ በቤኒሻነጉል ጉሙዝ ጥምረት የበለጠ ትኩረት ሰጥቶት
የሚሰራው በጎ ፈቃደኞችን በማበረታታት መሆኑን ሪፖርቱ ያመላከተ ሲሆን፤ በተጨማሪም በሰውነት ውስጥ ያለውን
የቫይረስ መጠን ወደማይታይ መጠን ማውረድ ዋናው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት የለው ጉዳይ መሆኑ ተብራርቷል፡፡ ሆኖም
ግን እነዚህን ተግባራት በሚፈለገው መጠን እንዳያከናውን የባለሞያ እጥረት እንዳለበት ጥመረቱ ገልጿል፡፡
ሁሉም ጥምረቶች ስራዎቻቸውን በሚሰሩበት ወቅት ያጋጠሟችን ተግዳሮቶች ያስቀመጡ ሲሆን፤ዋና ዋናዎቹም የተቀናጀ
እቅድ አለመኖር፤ጥራት ያለው ሪፖርት አለመቅረብ፤ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች አለመኖር እና የባለሞያ እጥረት እንዲሁም
የበጀት እጥረት እና አንዳንድ ቦታዎች ላይ የጸጥታ ችግሮች ናቸው፡፡ እነዚህን ተግዳሮቶች ለመቋቋምም የየራሳቸውን
እርምጃዎች እንደወሰዱ ጥምረቶቹ ገልጸዋል፡፡
ጥምረቶቹ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቶቻቸውን ማቅረባቸውን ተከትሎ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ምለሽና
ማበራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ለጥያቄዎቹና አስተያየቶቹ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት አቶ ካሳሁን ፤ በቀጣይ ሁሉንም ያሳተፈ
እቅድ እንደሚታቀድ እንዲሁም ሁሉም ጥምረቶች ተገናኝተው በመወያየት ወደ ፍጻሜ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡ ስልጠናን
በተመለከተ ሁሉም ጥምረቶች ለኬዝ ማናጀሮችና አድሄራንስ ሰፖረተሮች እንደሚሰጥ እንዲሁም የባለሞያ ስልጠናም
እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ ከህክምና የጠፉትን ወደ ህክምና መመለስን በተመለከተ ክፍያው ለአምጪው አሰራሩ በካስኬድ
እየታየ ፈላጊው ያደረገው ጥረት አና የሄደባቸው ሂደቶች በሚያቀርበው ሪፖርት በደንብ ተገምግመው መሆን አለበት
ብለዋል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ሶማሊ እና አፋር ክልሎች ትኩርት የሚፈልጉ ክልሎች ቢሆኑም እገዛ እንዳልተደረገላቸው
የገለጹት አቶ ካሳሁን፤ በቀጣይ ግን ማህበራትንም ጭምር ያሉበትን ሁኔታ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን የመቃኘት እቅድ
እንዳለም አብራርተዋል፡፡ በአቅም ግንባታ ደረጃም በትብብር እንሰራለን ብለዋል አቶ ካሳሁን፡፡ በቫይረሱ የሚያዙ ሴቶች
ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ድርጅቱ ወደፊት ከሴቶች ጥምረት ጋር በመሆኑ ሁሉም ጥመረቶች ትኩረት ሊሰጡት እንደሚገባም
አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት አቶ ካሳሁን ኔፕፕላስም ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡4

አቶ ካሳሁን ታደሰ እና አቶ በላይ ረታ ውይይቱን ሲ መ ሩ
በቀጣይ ከጤና ሚኒስቴር ከመጡ ተወካዮች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተወካዮቹ ከኔፕፕላስ የተወከሉ አባላት
የሚከተሉትን ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡ የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸው አካባቢዎች ላይ የማህበራት ቁጥር ቢጨመር፤
ለአደሄረንስ ሰፖርተሮችና ኬዝማናጀሮች የቁሳቁስ ዝግጅት ቢደረግ፤ለሰፖርቲቭ ሱፐርቪዠን በጀት ቢመደብ፤ህክምና
ያቋረጡትን በተመለከተ በርካታ ድርጅቶች ስለሚነቀሳቀሱ ድግግሞሽ አና የሃብት ብክነት እየተፈጠረ ስለሆነ ፈቃድ አስጣጡ
ቢፈተሽ፤ ለወጣቶች ልዩ ትኩረት ቢሰጥ እና በጀት ከመንግስት የሚያገኙበት ሁኔታ ቢመቻች፤ የሚሉት ናቸው፡፡ የጤና
ሚኒስቴር ተወካዮችም የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የመጀመሪያው ምላሽ ሰጪ አቶ ሃብታሙ ካሳ በፌደራል ኤች አይ ኢ መከላከል እና መቆጣጠር ጽ/ት ቤት የዘርፈ ብዙ ምላሽ
ዴሽክ ኃላፊ ሲሆኑ በምላሻቻም የጋራ እቅድን በተመለከተ ምንም አይነት አቅዶችም ሆኑ ሃገራዊ ዳሰሳዎች ሲዘጋጁ በጋራ
ነው፡፡ የተሰሩ ስራዎችም መገምግ ያለባቸው በጥምረት መሆን አለበት፡፡ ኔፕፕላስ የግሎባል ፈንድን በጀት ያውድድር
ለመውሰድ በመጀመሪያ ደረጃ ያንን መስራት የሚችል ቁመና ያለው ድርጅት መሆን ያስፈልጋል፡፡ ይሄንን እድል ለማግኘት
የመከላከል ስራ ላይ ትኩረት ያደረገ ተቋም ይኑራችሁ፡፡ ስራቸሁን በሚፈለገው መልኩ መስራት ከቻላቸሁ እና ካሳመናችሁ
እዚህ ደረጃ ላይ የማትደርሱበት ምክንያት የለም፡፡ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን በመርዳት ረገድ ከፍተኛ ተጽእኖ መፍጠር
ይኖርባችኋል፡፡ ቫይረሱ ያለባቸው ዜጎች ዩኒቨርሲቲ ሲመደቡ እዚያወ ባሉበት አካባባ እንዲመደቡ በማገዝ እንዲሁም ፤
ሰርተው መለወጥ ለሚፈልጉ ገንዘብ ከሚያበድሩ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቀላሉ ብድር አግኝተው ራሳቸውን እንዲጨሉ
በማድረግ በርካታ ስራዎችን መስራት ይጠበቅባችኋል፡፡
ኔፕፕላስ በምክር ቤት ውክልና ማግኘት ከቻለ በርክት ተጽኖ ፈጣሪ ውሳኔዎች እንዲወሰኑ የማድረግ አቅም ይኖረዋል፡፡ ቦታው
በመንግስት ላይ የተለያዩ ጫናዎችን ለመፍጠር ስሚረዳ በዚህ ላይም በርካታ ስራዎችን መስራት ይጠይቃል፡፡ የሃገር ውስጥ
በጀት ላይ ማተኮር የሚለው የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡ የውጪ እርዳትዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሱ ስለሚመጡ የሃገር
ውስጥ የሃብት ምንጮች ላይ ትኩረት ማድረግ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡5

ተሰብሳ ቢ ዎ ች በከፊል
አቶ ሐየሎም አሰፋ የCCM ኢትዮጵያ ተወካይ በሰጡት ምላሽ ኔፕ ፕላስ ከመንግስት በጀት እንዲበጀትለት የማድረጉ ስራ
ብሄራዊ ስትራቴጂክ እቅድ ውስጥ እንዲካትት በእቅድ ወቅት ይሰራል፡፡ ግጭት በሚፈጥርበት ወቅት ቫይረሱ ያለባቸው
ወገኖች ይበለጠ ተጋላጭ እንደሆኑ የተነሳውም የአቅዱ አንድ አካል እንዲሆን ጥረት ይደረጋል፡፡ ቀላል ስራ ስለማይሆን
ነገሮችን ማስተካከል እና መታገል ያስፈልጋል፡፡
በጤና ሚኒስቴር የኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ጽ/ቤት መሪ ስራ አስጻሚ የሆኑት አቶ ፈቃዱ ያደታ በሰጡት
ማብራሪያም መዋቅሮች ሲቀያየሩ ነገሮችን በነበሩነት ማስኬድ ይከብዳል፡፡ የክልል አመራሮች እዚህ ጋር የሚነሱትን
ጥያቄዎች በጥልቀት ልትመረምሩ እና አቅጣጫዎቹን ወደ ተግባር ልትቀይሩ ይገባል፡፡ ዝም ብሎ መስራት ብቻ ሳይሆን
ጊዜው የሚፈልገውን ስራ መስራት እና በፍጥነት ወደ ስራ መግባት ይጠይቃል፡፡ ከየቤተሰቡ ቫይረሱ በደማቸው ያለ ሰዎችን
ከያዝን ስርጭቱን በቀላሉ መቆጣጠር እንችላለን፡፡ ከተለመደው አስራር ወጣ ብሎ በመግባባት፣ አቅምን አሟጦ በመጠቀም
ነው ለውጥ ሊመጣ የሚቸለው፡፡ ኔፕፕላስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለ ኤች አይ ቪ መቆጣጠር እና መከላከል
የሚመደበውን የግሎባል ፈንድ በጀት መጠቀም አለበት፡፡ ይሄንን እድል ለመጠቀም ድርጅቱ ራሱ በሚፈለገው መልኩ
ማስተካከል እና ስራዎቹን በሚገባ ማከናወን ይኖርበታል፡፡ የቀድሞ እቅዶቻችሁን እንዳትደግሙ፡፡ የወጣቶችን ተጋላጭነት
በተመለከተ አሁን ላይ ያለው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ነው፡፡ ቀድሞ ዋና ዋና ተጠቂ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች አሁን ላይ ብዙ
ናቸው፡፡ ሴቶችን ከገጠር ወደ ከተማ የሚያመላልሱ ሰዎች፤ ከቤት እንኳን ወጥተው የማያውቁ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና
አፍላ ወጣቶች በጣም ተጋላጭ እየሆኑ ነው፡፡ እነዚህ ወጣቶች ስለ ኤች አይቪ የማያውቁ ናቸው፡፡ በቀጣይም እንደየ ክልሎቹ
ተጨባጭ ሁኔታ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን መድረስ ያስፈልጋል፡፡ አዲስ የመያዝ ምጣኔ አሁንም
ያልቀነሰው ከ15 እስከ 24 አመት ባሉት ላይ ነው፡፡ በት/ት ሚኒስቴር ውስጥ እንኳን ቀድሞ በተለያዩ ክበባት ይደረግ የነበረው
እንቅስቃሴ አሁን ላይ የለም፡፡ ይሄ ተመልሶ እንዲጀመር ተፅኖ ማሳደር አለባቸሁ፡፡ ወጣቶች ወደ ፕሮጀክት እንዲመጡ
ማድረግ እና ሃገር ውስጥ ሃብት ላይ በማተኮር በግጭት ወቅት መጠቀም ያለባችሁ ሜካኒዝም ላይ አስቀድማቸሁ ስሩ፡፡6

አቶ ሃብታሙ ካሳ ፈቃ ዱ ያደታ እና አቶ ሃየሎም አሰፋ ተሰብሳቢዎችን ሲያወያዩ
ቫይረሱ ያለባቸው ወጣቶች የስነልቦናና ማህበራዊ ስልጠና ላይ አተኩራችሁ ልትሰሩ ይገባል፡፡ ወደ ግንኙነት ሲገቡ መቋቋም
የሚችሉበት ሁኔታ ላይ አቅዳችሁ ከሰራችሁ እኛም እናግዛችኋለን፡፡ አማራ ክልል ያለው ችግር ተደራራቢ ቢሆንም በአዲስ
አበባ ዙሪያም የባሰ ችግር አለ፡፡ በተመሳሳይ በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እጅግ ከባድ ነው፡፡ የመድሃኒት እጥረት እንዳይኖር
ጥናትን መሰረት ያደረገ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ የመጀመሪያው 95 በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የመናውቀውም በጥናት ነው፡፡
የግብኣት ችግሮች ስላሉ የችግሩን መነሻ በማጥናት ላይ ነን ፡፡ መድሃኒት ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ በሚላክበት ሁኔታ ላይ
አብረን እንሰራለን፡፡ ክልሎች ሪቪው ሚቲንግ ሲያካሂዱ የጤና ሚኒስቴር ሃላፊዎች፤ የክልል ጤና ቢሮ ሃላፊዎች እና
ዳይሬክተሮች በተገኙበት መሆን አለበት፡፡ በዚያ መድረክ ላይ በሚገባ ተወያይቶ የተሻለ ስራ መስራት ይቻላል በማለት
ድርጅቱ ሊያግዙ የሚቸሉበትን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኢን ኢትዮዮጵያ (ኔፕ ፕላሰ) ማስታወቂያ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኢን ኢትዮዮጵያ (ኔፕ +) አሁን ያለውንና ከላይ የሚታየውን የድርጅቱን አርማ አሻሻሎ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
አዲሱ አርማ ማንጸባረቅ ያለበት ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

  • ድርጅቱ የጥምረቶች ጥምረት መሆኑን የሚያሳይ መሆን አለበት
  • በየክልሉ ኤች አይቪን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተቋቋሙ የየክልሉን ጥምረቶችን፤ ማሀህበራትንና ኤች አይቪ
    በደማቸው ያለባቸው ወገኖችን አንድነት ፤መተባበርንና አብሮ በቅንጅት መሥራትን የሚያሳይ መሆን ይገበዋል፡፡
  • ድርጅቱ ጾታን፤ ዘርን፤ ሐይመኖትን፤ የጤና ሁኔታና እና የመሳሰሉትን መሠረት በማድረግ አድሎና ማግለል
    የማያደርግና ለሰው ልጅ ሁሉ በተለይም በችግሩ ውስጥ ላሉ ክፍሎች በእኩልነት የቆመና የሚያገለግል መሆኑን
    የሚያሳይ

ኔፕፕላስ አዲስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ሾመ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን አትዮጵያ (ኔፕፕላስ) አዲስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ሾመ፡፡ የኔፕፕላስ ስራ አመራር ቦርድ የካቲት 1 አና 2 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ባካሄደው ስብሰባ ከቀረቡት አጩዎች መካከል አቶ ካሳሁን ታደሰን ባላቸው የስራ ልምድ፤ ክህሎት እና ብቃት ለቦታው ብቁ መሆናቸውን በማረጋገጡ የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟል፡፡ የኔፕፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱረሃማን ከማል እንደገለጹትም ለቦታው ከቀረቡት እጩዎች መካከል አቶ ካሳሁን ድርጅቱን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርጉት በመተማመን የስራ አመራር ቦርዱ በሙሉ ድምጽ የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟቸዋል፡፡

አቶ ካሳሁን ታደሰ አዲሱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር

አቶ ካሳሁን ታደሰ የትምህርት ዝግጅታቸውን ስንመለከት የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በማኔጅመንት ያገኙ ሲሆን፤ በቢዝነስ ደግሞ የማስተርስ ድግሪያቸውን ሰርተዋል፡፡ በተጨማሪም በፐብሊክ ኸልዝ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እና ጥናቶችን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ አቶ ካሳሁን በስራው አለም በአጠቃላይ ወደ 17 አመታት ልምድ ያላቸው ሲሆን፤ ከእንዚህ ውስጥም ዋና ዋናዎቹ የኢትዮ ላይፍ ሴቪንግ አሶሲየሽን መስራች እና ጀነራል ማናጀር ሲሆኑ በተለያዩ ትላልቅ ድርጅቶች ውስጥም በተለያየ የሃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል፡፡ ከእንዚህ ተቋማት መካክልም በኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ በኤክስኮዩቲቭ ዳይርክተርነት እንዲሁም በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማናጀርነት ፤ በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ አይ ካፕ ኢን ኢትዮጵያ በአድሄረንስ ሰፖርተርነት አማካሪ እና አድሄረንስ ኬዝ ማናጀመንት ፕሮግራም ኤክስፐርት ናቸው፡፡

ለዚህ ሃላፊነት መመጣቸውን ተከትሎ ድርጅቱን አሁን ካለበት ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የአጭር ጊዜ እቅዶችን መያዛቸውን የገለጹልን አቶ ካሳሁን ፤ ይሄንን ለማሳካተም የድርጅቱን የውስጥ አቅም ማደራጀት፤ የኔትዎርኩንና የክልል ኔትዎረኮችን አቅም በቴክኒክ፤ በእውቀት እንዲሁም በክህሎት ማጠናከር፤ ከለጋሾችና ከአጋር ደርጅቶች ጋር የነበረውንና የተቋረጠውን ግንኙነት መልሶ በማስቀጠል ሃብት የማበልጸግ ስራዎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ገልጸውልናል፡፡ ኔፕፕላስ ምንም እንኳን እውቅና የተሰጠው ትልቅ ድርጅት ቢሆንም በመንግስት በኩል እስካሁን ድረስ ፋይል ያልተከፈተለት በመሆኑ በቀጣይ ግን ፋይል ተከፍቶለት ጤና ሚኒስቴር በየአመቱ ከሚመደብለት በጀት ላይ አመታዊ በጀት እንዲመድብለት ለማድረግ በርካታ ስራዎችን የመስራት እቅድ እንዳላቸው እንዲሁም የደርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ፤ ፖሊሲ እና ስትራቴጂክ ፕላን ዘመኑን በዋጀ ምልኩ የመከለስ እና የማዘጋጀት ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል አቶ ካሳሁን፡፡

ምንም እንኳን እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን ለማከናወን በከፍተኛ ዝግጅት የመጡ ቢሆንም የተወሰኑ ተግዳሮቶች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ የገለጹት አቶ ካሳሁን፤ እነዚህን ችግሮች በተገቢው መንገድ ለመቋቋም መዘጋጀታቸውንም አስረድተዋል፡፡ የመጀመሪያው ሊገጥም የሚችለው ተግዳሮት የታሰበውን እና አስፈላጊውን ያህል ሃብት የማግኘት ችግር ሲሆን፤ ይሔ ችግርም በተለያየመልኩ ይፈታል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በድርጅቱ ውስጥም ሆነ በክልል ኔትዎርኮች ውስጥ ያለውን የጥቅም ግጭት ለመፍታት በቴክኒክ፤ በእውቀት እና በክህሎት የአቅም ማጎልበት ስራዎች ይሰራሉ እንደ አቶ ካሳሁን ገለጻ፡፡ ሌላው ሊገጥም ይችላል ያሉት ተግዳሮት ለጋሾች በየጊዜው መቀያየራቸው የየራሳቸውን ባሕሪ ይዘው ስለሚመጡ ያንን ጫና ለመቋቋምና ተመቅረፍ የሃገር ውስጥ ሃብት የማፈላለግ ስራም ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ክልሎች የተመደበላቸውን ሃብት በእግባቡ አለመጠቀም ሌላው ሊገጥም የሚችል ተግዳሮት መሆኑን የገለጹት አቶ ካሳሁን ይሄንንም በተለያየ መንገድ ለመቅረፍ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ኔፕፕላስ በሃገር አቀፍ ደረጃ ቫይረሱ ያለባቸውን በርካታ ወገኖች ያቀፈ ዣንጥላ አንደመሆኑ የግል ጥቅምን ሳይሆን የማህበረሰቡን ድምጽ ለማሰማት እና ቫይረሱ ያለባቸው ወገኖች የተሻለ ህክምና በማግኘት የተሻለ ህይወት እንዲኖሩ የሚረዳ፤ በመንግሽጽና በኅዝብ መካከል ድልድይ በመሆን የመንግስትንም ጫና የሚቀንስ ሃገር አቀፍ ድርጅት እንደመሆኑ; ሁሉም አካል በእኔነትና ይመለከተኛል በሚል ስሜት እጅና ጓንት ሆኖ በትብብር ሊሰራ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ ሁሉም በኔትዎርኩ ዙሪያ ያለ አካል አንድ በመሆን የግል ስሜትን ሳይሆን የማህበረሰቡን ጥቅም በማስቀደም እና በአገልጋይነት ስሜት ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም መክረዋል፡፡

በየጤና ተቋማት የሚሰሩ ኬዝ ማናጀሮች እና የአድሄረንስ ሰፖርተሮች በመንግስት መዋቅር እንዲካተቱ ሃሳብ ቀረበ

የኤች አይ ቪ ስርጭትን በመግታት እቅስቃሴ ውስጥ ላለፉት 11 አመታት ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የነበሩት ኬዝ ማናጀሮች እና የአድሄረንስ ሰፖርተሮች አስፈላጊነት ላይ ያተኮረ ዎርክሾፕ በቢሾፍቱ ከተማ ከመስከረም 10 – 11 ቀን፤ 2015 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ በውይይቱ መጨረሻም ሰራተኞቹም በመንግስት አስተዳደር ኮሚሽን እንዲታቀፉ ሃሳብ ቀርቀቧል፡፡ በዎርክሾፑ ላይም የኔፕ ፕላስ ቦርድ አባላት ፤የፌድራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተወካዮች ፣ የጤና መድህን አገልግሎት ባለሞያዎች ፤ የጤና ሚኒሰቴር ተወካዮች ፤ የክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተወካዮች፤ የየክልል ጤና ቢሮዎች ተወካዮች፤ አንዲሁም የተለያዩ አካላት ተሳትፈዋል፡፡


የዎርክሾፑ ተሳታፊዎች በከፊል
በዎርክሾፑ መክፈቻ ላይ የኔፕፕላስ ተ/ዳይሬክተር አቶ ባይሳ ጫላ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ኔፕፕላስ ባለፉት 11 አመታት ኤች አይ ቪ በደማቸው ያለባቸውን ዜጎች በማሰማራት በተለያየ መልኩ ህብረተሰቡን የጠቀመ መሆኑን አስረድተው፤ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ለምሳሌ የሚቀርቡ ናቸው ብለዋል፡፡ አሁንም ሲዲሲ ለዚህ ስራ ይሰጠን የነበረው በጀት ቢያቆምም በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አቶ ባይሳ በንግግራቸው አንስተዋል፡፡

በአሁን ወቅት በሃገሪቱ ያለውን የኤች አይ ቪ ሁሄታ በተመለከተ የጤና ሚኒሰቴርን ወክለው ጽሁፍ ያቀረቡት አቶ ደስታ ሞገስ ሲሆኑ፤ በጽሁፋቸውም በየአመቱ ከ 1ነጥነብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በኤች አይ ቪ ቫይረስ የሚያዙ ሲሆን፤ በዚሁ ምክንያትም 680 ሺ ዜጎች ህይወታቸው ያልፋል ብለዋል፡፡ በቀረበው ጽሁፍ እንደተቀመጠው ከእነዚህም ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ሴቶች ሲሆኑ፤ በዚህም መሰረት 19 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሴቶች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኘ ተገልጿል፡፡ የወንዶችን ቁጥር ስንመለከት ደግሞ 16 ነጥብ 7 ሚሊዮን ወንዶች የኤች አይ ቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ይገኛል፤ እንደ ጽሁፉ፡፡ በኤች አይ ቪ ቫይረስ ምክንያት የሚሞቱ ወገኖች ቁጥርን ስንመለከትም በቀላሉ የሚታይ አይደለም ያሉት አቶ ደስታ፤ በዚሁ ምክንያት በየአመቱ 640ሺ ወንዶች እና 240 ሴቶች ህይወታቸው ያልፋል ብለዋል፡፡
የቫይረሱን ስርጭት በእድሜ ስብጥር ስንመለከተው በ2021 በነበረው መረጃ መሰረት በየአመቱ አድሜያቸው ከዜሮ እስከ 14 አመት የሆነ 150 ሺ ህጻናትና ታዳጊዎች በቫይረሱ የሚያዙ ሲሆን፤ በዚሁ ሳቢያም 99ሺ ሕጻናትና ታዳዎች በሞት ይቀጠፋሉ፡፡ በክልል ደረጃ ያለውን የቫይረሱን ስርጭት በተመለከተም መረጃው እንዳስቀመጠው በ2021 አማራ ክልል፤ ኦሮሚያ እንዲሁም አዲሰ አበባ በቅደም ተከተል ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ካደረጉት ምክንያቶች መካከልም በተለይ ሴቶች ስለቫይረሱ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ መሆን፤ ኮንዶምን በአግባቡ አለመጠቀም፤ ጾታን መሰረት ያደረጉ ተግባራት አሁንም ድረስ እየተተገበሩ መሆኑ እንዲሁም የወሲብ ንግድ መስፋፋት ናቸው፡፡
የአቶ ደስታን ማብራሪያ ተከትሎ የኔፕፕላስ ፐሮገራም ማናጀር አቶ ድንቁ ወርቁ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ምንነት እና አስፈላጊነት የሚገልጽ ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን፤ በጽሁፋቸውም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በጤና ተቋማት እና በማህበረሰቡ መካከል የሚኖረው አገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን ከፍተኛውን ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በማህበረሰቡ እና በጤና ተቋማት ዘንድ ያለውን ሀብት በአግባቡ አሟጦ መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያላቸው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑ አብራርተዋል፡፡ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች ከሚሰጧቸው አገልግሎቶች ዋና ዋናዎችም ዜጎች የኤች አይ ቪ ምርመራ እንዲያደርጉ የምክር አገልግሎት መስጠት ፤ ከራሳቸው ተሞክሮ ተነስተው ያለውን ሁኔታ በግልጽ በማስረዳት ቫይረሱ በደማቸው ያለ ዜጎች ህክምና እንዲጀምሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም ህክምናውን ያቋረጡ ዜጎች ወደ ህክምናው እንዲመለሱ የተለያዩ ጥረቶችን ማድረግ ተጠቃሾች መኆናቸን አቶ ድንቁ ጨምረው አብራርተዋል፡፡

የዎርክሾፑ አወያዮች

ሌላው የኬዝ ማናጀሮችና ደሄረንስ ሰፖረተሮች ስራ ያስገኛቸው ውጤቶችና የጋጠሙ ችግሮችን በተመለከተ ጽሁፍ ያቀረቡት የኔፕፐላስ ምዘናና ግምገማ ባለሞያ አቶ ቢኒያም ወርቁ ሲሆኑ፤ በጽሁፋቸውም ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሚሰሯቸው ስራዎች በርካቶች ቫይረሱ በደማቸው ያለ ዜጎች ህክምናቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ እና ህክምና ባለማግኘታች ሊደርሱ የሚችሉ ችግሮችን ማስቀረት መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ለአብነት ያህልም በ2020 እና በ2012 ብቻ ህክምናቸውን ካቋረጡ ከ80ሺ በላይ ወገኖች መካከል ከ40ሺ በላይ የሚሆኑት ወደ ህክምና እንዲመለሱ ማድረግ ችለዋል ብለዋል አቶ ቢኒያም ፡፡በተጨማሪም በኬዝ ማናጀሮች እገዛ እየተደረገላቸው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ከራሳቸው አልፈው ቤተሰቦቻቸው የኤች አይ ቪ ምርምራ እንዲያደርጉ በማሳመን እና ወደ ምርመራ ቦታ በማምጣት ሥራው ላይ እንዲሳተፉ ማድረጋቸውን አቶ ቢኒያም በማብራሪያቸው ገልጸዋል፡፡
የኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖረትሮች የሚሰጡት አገልግሎት በርካታ ቢሆንም፤ ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይወጡ የሚደርጓቸው በርካታ ችግሮች መኖራቸውንም አቶ ቢኒያም አስረግተዋል፡፡ ከእነዚህ ችግሮች መካከልን እንደ እሳቸው ገለጻ ዋና ዋናዎቹ የምክክር አገሎገሎት ለመስጠት የሚመቹ ገለልተኛ ክፍሎች አለመኖር፤ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰርቪስ ስር ባለመታቀፋቸው ልዩ ልዩ ጥቅማ ጥቅሞች ማግኘት አለመቻላቸው፤ ከጤና ተቋማት ደጋፍ በተገቢው መንገድ ማግኘት ነጻ ህኪምና ማግኘት አለመቻላቸው እንዲሁም ዝቅተና ደመወዝ ተከፋይ መሆናቸው እና የፕሮጀከቶች ስራ በጊዜ የተገደበ መሆን ተጠቃሾቹ ናቸው ብሏል አቶ ቢኒያም፡፡
ከየተቋማቱ የመጡ ተሳታፊዎች በየዘርፋቸው 20 የደቂቃ ገለጻዎችን ያደረጉ ሲሆን፤ በዋናነት ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮችም የኤች አይ ቪ አሁናዊ ተጨባጭ ሁኔታ፤ የኬዝ ማናጀሮች አስፈላጊነት፤ የሚሰሯቸው ስራዎች አንዲሁም ስራዎቻቸውን በሚሰሩበት ወቅት የሚገጥሟቸው ችግሮች አና ችግሮቹን ለመፍታት የተጓዙባቸውን መንገዶች የሚያስረዱ መረጃዎች ለተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡
ከዚህ በመቀጠልም እያንዳንዱ ክልል የየራሱን ተሞከሮ ያቀረበ ሲሆን፤ የአማራ ክልል ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰርቪስ ስር እንዲካከቱ በማድረጉ ችግሩን ከሞላ ጎደል መቅረፍ መቻላቸውን ተወካዩ አስረድተዋል፡፡ ሌሎችም በቀጣይነት ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች በሲቪል ሰረቪሱ ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወገኖች በጤና መድህን ሊታቀፉ የሚችሉበት እና ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት በሚቻልበት መንገድ ላይም ማብራሪያ ቀርቧል፡፡ ከኢትጵያ ጤና መድን አገልግሎት ተወካይ አቶ ጉደታ አበበ በአሁኑ ወቅት ያለውን የጤና መድን ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ እንደ አቶ ጉደታ ማብራሪያ የጤና መድን አገልግሎት ለሁሉም ዜጋ መዳረሱ እንደ ግዴታ ሊወሰድ ስለሆነ ማንም ከዚህ አገልግሎት ውጪ ሊሆን አይችል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉም ዜጋ በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድን አሊያም በማህበራዊ ጤና መድህን እንዲታቀፍ የሚያስገድድ ህግ ተግባራዊ ሥለሚደረግ በዚህ ሂደት ውስጥ ቫይረሱ በደማቸው ያለባቸው ዜጎችም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አቶ ጉደታ ጨምረው አስረድተዋል፡፡
በውይይት መድረኩ በተለይ ኬዝ ማናጀሮችና አድሄረንስ ሰፖርተሮች የቫይረሱን ስርጭት በመግታት ረገድ ያላቸው ጠቀሜታ የጎላ መሆኑ ከግምት ውስጥ ገብቶ በሲቪል ሰርቪሰና በጤና መድን ስር ታቅፈው አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ እና እያንዳንዱም የየራሱን ሃላፊነት ለመወጣት ቃል በመግባት ስብሰባው ተጠናቋል፡፡

አድሎና ማግለል ጥናት ላይ ውይይት ተካሄደ

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭሰ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) በመድሎና ማግለል ላይ
ከህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጋር ውይይት አካሄደ
ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ) በኤች
አይ ቪ ምክንያት በሚደርሰው አድሎና ማግለል ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማህበራዊ
ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴጋር ነሃሴ 2 ቀን 2014 በቢሾቱ ኪሎሌ ሆቴል ውይይት አካሂዷል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይም የተለያዩ አካላት ንግግር አድርገዋል፡፡


የውይይቱ ተሳታፊዎች በከፊል

በውይይቱ ቋሚ ኮሚቴውን በመወከል ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ ሲሆኑ፤
እሳቸውም በገለጻቸው በኤች አይ ቪ ተጽእኖ ላይ እንዲህ አይነት በቁጥር ላይ የተመሰረተ
ጥናት መቅረቡ በጉዳዩ ላይ የበለጠ ስራዎችን ለመስራት የሚኖረው ጠቀሜታ የላቀ መሆኑን
አብራርተዋል፡፡ በግምት ብቻ የሚሰሩ ስራዎች የተፈለገውን ውጤትለማስገኘትም ሆን
በህብረተሰቡ ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚደረገው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ይፈጥራል
ብለዋል ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ ፡፡ በዚህ መልኩ ተጨባጭነት ያለው ጥናት መደረጉ በጉዳዩ
ላይ የበለጠ ለመስራት የሚፈልግ ሌላ አካል እንኳን ቢኖር ጥሩ መነሻ የሚሆንና
በማህበረሰቡ ውስጥም ለውጥ ለማምጣት የሚያግዝ መሆኑን ወ/ሮ ወርቅሰሙ ጨምረው
ገልጸዋል፡፡


ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ
ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ተወክለው የመጡት ወ/ ሮ ምርቴ ጌታቸው በበኩላቸው ሚኒስቴር
መስሪያ ቤቱ የኤች አይ ቪ ስርጭት አና የሚከሰቱት ተያያዥ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ብዙ
ስራዎችን እየሰራ መሆኑን በመግለጽ፤ እንዲህ አይነት ጥናቶች መካሄዳቸው ስራውን የበለጠ
ለማቀላጠፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አብራርተዋል፡፡ ባለፉት አመታት በኤች አይ ቪ
ምክንያት የሚከሰት ሞትን በ 53በመቶ እንዲሁም የቫይረሱን ስርጭት 87 በመቶ መቀነስ
ተችሏል ያሉት ወ/ሮ ምርቴ፤ የኤች አይ ቪ ህክምና ሽፋኑ 93 በመቶ እንዲሁም ቫይረሱን
የመቆጣጠር አቅም ወደ 96 በመቶ ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል ተወካዩዋ፡፡ ተመርምሮ
ራስን ማወቅን በተመለከተም በአሁኑ ወቅት 84 በመቶ የሚሆኑት ወገኖች ተመርምረው
ውጤታቸውን ያወቁ ሲሆን፤ በተቃራኒው ደግሞ 16 በመቶ የሚሆኑት በተለያዩ ምክንያቶች
ምርመራ እንዳላደረጉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ተመርምረው ራሳቸውን እንዳያውቁ
ከሚያደርጓቸው ምክንያያቶች መካከልም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሊደርስባቸው
የሚቸለውን መድሎና መገለል በመፍራት መሆኑንም አብራርተዋል ፡፡ በአሁኑ ሰአትም ከ
1500 በላይ የሚሆኑ የኤች አይ ቪ ህክምና መስጫ ጣቢያዎች እንዲሁም ከ4000 በላይ የ
ኤች አይ ቪ የምርመራ ጣቢያዎች እንዳሉም አብራርተዋል ወ/ሮ ምርቴ፡፡


ወ/ሮ ምርቴ ጌታቸው

እንግዶች ያደረጉትን ንግግር ተከትሎም የጥናቱን አስፈላጊነት፤ አላማ እና አካሄድ
በተመለከተ የኔፕ ፕላስ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የጥናቱ የቴክኒክ ኮሞቴ ሰብሳቢ አቶ
ጌታቸው ጎንፋ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ጥናቱን ማድረግ የተፈለገበት
ምክንያት በኤች አይ ቪ ምክንያት የሚደርስ መድሎና መገለል ያለበትን ደረጃ አና ሁኔታ
ለማውቅ ፤ በመድሎና መገለል እና በኤች አይ ቪ አገልግሎት መካከል ስላለው ግንኙነት
ለመገምገም እንዲሁም በመድሎና መገለል ምክንያት የሚደርሰውን አሉታዊ ተጽእኖ ማቃለል
በሚቻልበት ሁንታ ላይ ምክረ ሃሳብ ለማስቀመጥ እንደሆነ አቶ ጌታቸው በገለጻቸው
ጠቁመዋል፡፡
የዳሰሳ ጥናቱን ለማድረግም የተለያዩ አባላት ያሉት ኮሚቴ ተዋቅሮ እንደነበረ እንዲሁም
በሂደቱ የተለያዩ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ዘዴዎች መከተላቸውን ገልጸዋል፡፡ ጥናቱ
ደረጃውን የጠበቀ እና ተአማኒነት ያለው እንዲሆንም በዘርፉ ልምድ ያላቸው የጥናት ተቋማት
ያስቀመጧቸውን ያሰራር ሂደቶች በመመልከት እና በመከተል መሰራቱም በመድረኩ
ጨምረው አብራርተዋል፡፡

አቶ ጌታቸው ጎንፋ
በመቀጠልም የጥናቱ ቴከኒካል ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩዬ
ዳመጠው አጠቃላይ የጥናቱን ውጤት ጠቅለል ባለ መልኩ አቅርበዋል፡፡ በማብራሪያቸወም
ከጠናቱ ተሳታፊዎች መካከል ምን ያህሉ የኤች አይ ቪ ውጤታቸውን ለሌሎች አካላት
አሳውቀዋል በሚል የጀመረው የወ/ሮ ጥሩዬ ገለጻ፤ በዚህ ጥናት ላይ ከተሳተፉ ሰዎች መካክል
84 በመቶዎቹ የኤች አይ ቪ ውጤታቸውን ቢያንስ በአካባቢያቸው ለሚገኝ አንድ ሰው
መግለጻቸውን ያመለክታል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ 16 በመቶ የሚሆኑት የኤች አይ ቪ
ውጤታቸውን ለማንም ሰው ያልገለጹ መሆናቸውን ምክትል ሰብሳቢዋ አክለው ገልጸዋለ፤፡፡
በተጨማሪም 23.4 በመቶዎቹ የጥናቱ ተሳታፊዎች የ ኤች አይ ቪ ውጤታቸው
ያለፍቃዳቸው የተገለጸባቸው ፤ 19.7 በመቶዎቹ ደግሞ የ ኤች አይ ቪ ውጤታቸውን
ያሳወቁት በተለያዩ ምክንያቶች ተገደው እንደሆነ የጥናቱ ተሳታፊዎች መግለጻቸውን
አብራርተዋል፡፡ ውጤታቸውን ይፋ እንዲያደርጉ ያሰገደዷቸው ነገሮችም የፍቅር እና የትዳር
ጓደኛ ለመያዝ፤ የተለያዩ እገዛዎችን ለማግኘት አና ለመሳሰሉት ምክንያት እንደሆነ የጥናቱ
ተሳታፊዎች አብራርተዋለ፡፡

ወ/ሮ ጥሩዬ ዳምጠው
የቀረበው መረጃ እንደሚጠቁመው በ ኤች አይ ቪ ምክንያት የሚመጣ መድሎና
መገለል ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ዜጎች ላይ አዎንታዊ አና አሉታዊ ተጽእኖዎችን
ያስከትላል፡፡ 45 በመቶ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች እንደገለጹትም በኤች አይ ቪ
ውጤታቸው ምክንያት የደረሰባቸው መድሎና መገለል በሕይወታቸው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ
አሳደሮባቸዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ እንደገለጹትም በተደረገባቸው መድሎና መገለል ሳቢያ በራስ
መተማመናቸውን እንዲያጡ፤ ጭንቀትን መቋቋም እንዲያቅታቸው ብሎም የፍቅር ጓደኛ
እንኳን መያዝ እንዳይችሉ አድርጓቸዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ልጅ ለመውለድ
የነበራቸውን ተስፋ እንዳሳጣቸው ገልጸዋል ተብሏል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ 44 በመቶ
የሚሆኑት ተሳታፊዎች በ ኤች አ ይ ቪ ውጤታቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ያለው
መድሎና መገለል የበለጠ በራሳቸው አንዲተማመኑ በማድረግ፤ ጭንቀታቸውን እንዲቋቋሙ
በማገዝ እንዲሁም ጠንካራና ተስፈኛ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ በአዎንታዊ መንገድ
እንደረዳቸው ተጠቁሟል፡፡
የጥናት ውጤቱ አጠቃላይ ዳሰሳ ከቀረበ በኋላም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች አና
አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን፤ ለጥያቄዎቹ ምላሽ እና ማብራሪያዎች ከአቅራቢዎች
ተሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም ተሳታፊዎች የየራሳቸውን አስተያያት አና ጥቆማ በመስጠት እና
ሰፊ ውይይት በማድረግ የውይይት መድረኩ ተጠቃሏል፡፡

የኔፕ ፕላሰ 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ

የኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይ ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕ ፕላስ) 17ኛ
መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ግንቦት 1 እና 2 ቀን 2014 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ከረዩ ሂል ሪዞርት
ሆቴል ተካሂዷል፡፡
በጉባዔው መክፈቻ ላይ የኔፕ ፕላስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ባይሳ ጫላ ባደረጉት ንግግር፤
ኔፕ ፕላስ ላለፉት 17 አመታት ከተለያዩ አካላት ጋር በመቀናጀት ከ200 ሺህ በላይ ቫይረሱ
በደማቸው የሚገኝ ወገኖች በማህበር ተደራጅተው አድሎና መገለል እንዲቀንስና ለሀገራዊ
ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ፤
ማህበረሰቡም ራሱንና ቤተሰቡን ከወረርሽኝ እንዲጠብቅ እንዲሁም እንደአስፈላጊነቱ ራሳቸውን
ይፋ በማውጣት ትምህርት እንዲሰጡ የማድረግ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በ 2030 ሊደርስበት ያስቀመጠውን የ 95 ፤ 95 ፤ 95 እቅድ
ተግባራዊ ለማድረግ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ወገኖች ከጸረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት ጋር
እንዲቆራኙ ወይም የህክምና ክትትላቸውን እንዲያጠናክሩ እንዲሁም መድሃኒቱን ጀምረው
ያቋረጡ ወገኖች በአፋጣኝ ወደ ህክምና ክትትል እንዲመለሱ የማድረግ ስራ በመሰራት ላይ
ይገኛል ብለዋል አቶ ባይሳ፡፡
የኔፕፕ ፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብድርሃማን ከማል በበኩላቸው፤ ለአዲሱ
የግሎባል ፈንድ ውድድር በቂ ዝግጅት በማድረግ ውጤታማ ሆኖ ለማሸነፍ መቻሉን
አብራርተዋል፡፡ ከአለፈው ጠቅላላ ጉባዔ ወዲህ ባለው ስራቸው ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን
ሰብሳቢው ሲገልጹም ፤ ወቅቱን ያልጠበቀ የሲዲሲ በጀት መቋረጥ፤ በርከት ያሉ ሰራተኞች
ስራቸውን መልቀቅ እና የበጀት እጥረት ዋናውናዎች መሆናቸውን አስቀምጠዋል፡፡ እነዚህን
ቸግሮችም በተለያየ መልኩ ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች መደረጋቸውን ሰብሳቢው ጨምረው
ገልጸዋል፡፡ የስራ አመራሮችን በተመለከተም የአመራርነት ሃላፊነታቸውን ያልተወጡትን
የብሄራዊ ጥምረቱ ስራ አስኪያጅ በአዲስ ተወካይ ቦርዱ መተካቱን ሰብሳቢው ጨምረው
ገልጸዋል፡፡
የበመቀጠል ጠቅላላ ጉባዔው የተጓደሉ እና ጊዜያቸውን የጨረሱ የጠቅላላ ጉባዔ
አመራሮች ምርጫ በህገ ደንቡ መሰረት አካሂዷል፡፡ ጉባዔው በሶስቱ አስመራጭ ኮሚቴ
አባላት አማካይነት አዲስ አመራሮችን የመረጠ ሲሆን፤ በዚህም መሰረት አቶ ማሙሸ ንጉሴ
የጠቅላላ ጉባዔ ሰብሳቢ ፤ወ/ሮ እቴነሽ እሸቴ የጠቅላላ ጉባዔ ም/ሰብሳቢ እንዲሁም አቶ ሙሴ
ማማጫ የጠ ቅላላ ጉባዔ ጸኃፊ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
በተጨማሪም በድርጅቱ በቦርድ አባልነት ከሀረሪ ክልል፤ ከአዲስ አበባ እና ከሴቶች
ጥምረት የተወከሉትን 3 የክልል ተወካዮችን ጉባዔው በቦርድ አባልነት እንዲሰሩ ጉባዔው
ያጸደቀ ሲሆን፤ በተገጓደሉ ጠቅላላ ጉባዔ አባልነትም የጋመቤላ ክልል ወክሎ የላከው 1፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የላካቸው 2 እና ሴቶች ጥምረት የላካቸው 4 ተወካዮችን
አጽድቋል፡፡
ጠቅላላ ጉባዔው በመቀጠልም በ2021 የተሰሩ ስራዎችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን፤
በመጀመሪያ የስራ አመራር ቦርዱን ሪፖርት በዝርዝር አይቷል፡፡
በቦርዱ ሪፖርት ላይ ከአባላት የተለያዩ ጥያቄናዎችና አስተያቶች የተነሱ ሲሆን፡
ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የቦርዱ ሰብሳቢው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡ ሰብሳቢው
በምላሻቸውም የተቋረጠውን የሲዲሲ ፕሮጀክት በተመለከተ ፕሮጀክቱን ለመመለስ ጥረት
እንደሚደረግ፤ የኔፕ ፕላስ በጀት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ በመሆኑ የድርጅቱ መመሪያዎችና
ደንቦችን በዚያ መልኩ እንደሚቃኝ አስረድተዋል ፡፡ የግሎባል ፈንድ አሰራሩ በአጠቃላይ
ስለተቀየረ የበጎ ፈቃደኞችን እና ሌሎች ሰራተኞችን አለማካተቱን የገለጹት ሰብሳቢው፤
በተጨማሪም በጦርነት የተጎዱ ክልሎችንና ሌሎች ድጋፍ የሚፈልጉ ማህበራትን ለመደገፍ
ቦርዱ ከ ጽ/ቤቱ ጋር የጋራ እቀድ አቅዶ እንደሚንቀሳቀስ ገልጸዋል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው ቦርዱ
ስራውን በአግባቡ እያከናወነ መሆኑን የተገነዘበ ሲሆን ፤ ለሚቀጥለው አመት የሃብት ማበልጸግ
ስራ እንዲሁም የውጪ የቦርድ አባላትን የማካተቱ ስራ ትኩረት ተሰጠቶ እንዲሰራ የውሳኔ
አቅጣጫ ሰጥቷል፡፡
ቀጥሎ ለጠቅላላ ጉባዔው የጽ/ቤቱ የ2021 ሪፖርት በክትትልና ምዘና መምሪያ ሃላፊው
በአቶ በላይ ረታ የቀረበ ሲሆን ፤ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ በላይ
ማብራሪያ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል ከ 150 ሺህ በላይ ለሆኑ ቫይረሱ በደማቸው ላለባቸው
ወገኖች በጸረ ኤች ኤቪ ህክምና ቁርኝት፤ በቫይረስ መጠን ልኬት ፤ በጸረ ኤች አይቪ ህክምና
ቅድመ ዝግጅት፤ ቤተሰብና የጾታ አጋሮቻቸውን በማስመርመር ፤ ከኮቪድ 19 በመከላከል እና
በአጠቃላይ ጤና አጠባበቅ ዙሪያ የግንዛቤ ማዳበሪያ ድጋፍ እንደተሰጣቸው ተብራርቷል፡፡
ከቀረበው ሪፖርት መረዳት እንደተቻለውም ድርጅቱ በኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት መቀነስ እና
መድሎና መገለል እንዲቀንስ በማድረግ እንዲሁም ከጸረ ኤች አይቪ መድሃኒት ጋር ያለውን
ቁርኝት በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡
አባላቱ ሪፖረቱ ካደመጡ በኋላም ፈንድ ለማግኘት ከመንግስት ጋር ያለው ቁርኝት ምን
ይመስላል፤ እንዲሁም የኔፕ ፕላስ የ 5 አመት መሪ እቅድ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ የሚሉና
የመሳሰሉ ጥቄዎችን አንስተዋል፡፡ ለጥያቄዎቹም ከድርጅቱ ጽ/በት ማብራሪያዎች
ተሰጥተዋለ፡፡
በተጨማሪም የኔፕ ፕላስ የ 5 አመት ስትራቴጂክ እቅድም ተገምግሞ መጠናቀቁን
እና ሴቶችና ሴቶች ጥምረትን ለማገዝ በጽ/ቤቱ በኩል ጥረት እየተደረገ መሆኑንም
ተብራርቷል፡፡
ከዚህ በመቀጠል ጠቅላላ ጉባዔው የ2022 እቅድን ያደመጠ ሲሆን አባላቱም ግሎባል ፈንድ
ፈጻሚ ያልሆኑ አባላት ጉዳይ በእቅዱ ቢካተት፤ በጦርነት የተጎዱ ማህበራትና ሴቶች በተለየ
መልኩ የሚደገፉበት መንገድ ቢመቻች በማለት አሳስበዋል፡፡ጠቅላላ ጉባዔው ሪፖረቱንና
እቅዱን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡በመጨረሻም ጠቅላላ ጉባዔው የ2021 የውጭ ኦዲት
ሪፖረተን ካደመጠ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

NEP+ Provided Refresher training for Case managers and adherence Supporters

(February 26 2022 Pr and Communication Department)

NEP+ Provided refresher training for 814 ( male 199 and female 615) case managers and adherence support drawn from dsellected health facilities found in SNNP, Sidama, South west , Oromia, Gambella Regions and Addis Ababa City Administration.
According to the information from NEP+ program Department, the training was focused on Mental Health Illness screening, Cervical Cancer ,prevention, key messages on viral Undetected leads to Un transmitted HIV during sexual intercourse and finally on the revised data management tools. The training was given in 6 round for 2 days each
The training was given at Adama, Jimma, Bishoftu and Butt Jira Towns within three month time from December 2021 to February, 2022.

Trainees in partial.
Trainees in partial.

Sample Text

About NEP

The NEP+, formerly known as AELWHA (Association of Ethiopians Living with HIV/AIDS), is established in October 2004 to raise and relay the collective voice of people living with HIV.

GPS Location of NEP+ Office

Contact Us

Address: Mexico Chamber of Commerce building 5th floor.
Phone: +251 111 659 1414/1818/1919
Fax: +251 111 659 1010
P.O.Box: 780 Code-1250
Email: eshetu@nepplus.org / aelwha@ethionet.et