ኔፕ ፕላስ 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት አካሄደ

ኔፕ ፕላስ 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት አካሄደ ኔትወርክ ኦፍ ኔትወርክስ ኦፍ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕ ፕላስ) 16ኛ መደበኛ
ጠቅላላ ጉባኤውን በባህርዳር ከተማ ከመጋቢት 23 እስከ 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታሪኩ በላቸው ሲሆኑ በንግግራቸው ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኤች.አይ.ቪ/ ኤድስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሶስት 90ዎች ፕሮግራም ወደ ሶስት 95ቶች መለወጡን አስታውሰው በተለይ በአሁኑ ሰኣት በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያውን 95 ለማሳካት ሰፊ እንቅስቃሴ በተጀመረበት ወቅት ይህ ታላቅ ጉባኤ መካሄዱ ለፕሮግራሙ መሳካት ሰፊ አበርክቶ እንደሚኖረው እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
አቶ ታሪኩ በላቸው የአማራ ክልል ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ታሪኩ አያይዘውም ዓለምን እየፈተነ ያለው የኮቪድ 19 ወረርሽን ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን
ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚደረገውን ዘመቻ አስቸጋሪ እንዲሆን እያደረገው ካሉ በኋላ በኢኮኖሚ ጠንካራ ያልሆኑና አንስተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ሴቶች እህቶቻችን የኮሮና ወረርሽኝ ኑሯቸውን እጅግ አስቸጋሪ አድርጎባቸዋል፡፡

በተለይ ይህ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የኤች.አይ.ቪ ስርጭት እንዲጨምር በማድረግ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ እንዳለም የሚያመለክቱ መረጃዎች እንዳሉ የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ምክትል ቢሮ ኃላፊው በንግግራቸው መጨረሻም ጉባኤው በእቅዶቻቸው ላይ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የመከላከል ስራን እንዲካትቱ ጥሪ አድርገው የአማራ ክልል መንግስት ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን በመከላከል ረገድ ለሚደረጉ ጥረቶች አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ ድጋፍ ለመስጠት ከክልሉም ሆነ ከብሄራዊ ጥምረቱ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ ንግግራቸውን አገባደዋል፡፡ ከመክፈቻው ንግግር ቀደም ብሎ የኔፕ ፕላስ ዋና ስራ አስኪጅ ለተሰብሳቢዎቹ ባሰሙት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ኔፕ ፕላ ባለፈው የፈረንጆቹ አመት በርካታ ስኬታማ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡ በንግግራቸውም ኔፕ ፕላስ ከሲዲሲ እና ከግሎባል ፈንድ ውጪ ከሌሎች ለጋሽ ድርጅቶች የገንዘብና የአይነት እንደዚሁም የቴክኒክ ድጋፎች ማገነቱን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ በተለይ ለደርጅቱ ችግር ሆኖ የመጣው መላው አለምን ፈታኝ የሆነው የኮቪድ 19 ክስተት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

አቶ መኮንን አለሙ የኔፕ ፕላስ ዋና ዳይሬክተር ለጉባኤተኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ሲያደርጉ ይህንኑ ወረርሽኝ ለመከላከልም ኔፕ ፕላስ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝና ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችሉ የእጅ ማጽጃና የፊት መሸፈኛ ማስኮችን በድጋፍ መልክ ማግኙቱን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የድርጅቱ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ እድላም ገ/ስላሴ በበኩላቸው ቦርዱ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መደበኛ እና አስቸኳይ ስብሰባዎችን በማካሄድ የኔፕ ፕላስ የስራ ግምገማ በማድረግ በታዩ ክፍተቶች ላይ የማስተካከያ አቅጣጫዎችና የቅርብ ድጋፍ ሲያደርግለት መቆየቱን አስታውሰው ከዚህ ውጭ በአንዳንድ የክልል ጥምረቶች ላይ በታዩ ችግሮች ላይ በቦታው ድረስ በመገኘት የመፍትሄ ሀሳቦችን ተሰጥተዋል ብለዋል፡፡ አቶ እድላም ገ/ሥላሴ የኔፕ ፕላስ ቦርድ ሰብሳቢ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት በሶስት ቀናት ቆይታቸው የድርጅቱን የቦርድ ሪፖርትና እቅድ፣ የጽቤቱን ሪፖርትና እቅድ፣ የኦዲት ሪፖርት እና አዲሱን የመተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል፡፡

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች አይቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ (ኔፕፕላስ)

ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች
አይቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ
(ኔፕፕላስ)

  • ኤች.አይ.ቪ ኤድስን ለመከላከልና
    ለመቆጣጠር የበጎ ፈቃደኞች ስንቅ
    ሀ/ መግቢያ
    ኤች.አይ.ቪ ኤድስ በአለም ላይ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የበርካታ
    ሰዎችን ህይወት ከመቅጠፉም በተጨማሪ ዛሬም ድረስ በርካታ ዜጎች
    ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅትም
    የሚከተሉት እውነታዎች ይስተዋላሉ፡፤
    1. ይህ ወረርሽኝ አሁንም በአለም ላይ ዋንኛ የጤና ችግር
    ሲሆን ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እንደ እ.አ.አ ዲሴምበር
    2018 መጨረሻ ድረስ ከ32 ሚሊዮን ህዝብ በላይ
    ህይወት እንደሳጣ እና ከ37.9 ሚሊዮን ህዝብ በላይ
    ደግሞ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡
    2. በአለም አቀፍ ደረጃ በተሰጠው ትኩረት ምክንያት
    በሽታውን የመከላከሉና የመቆጣጠሩ ስራ እንዲሁም
    አገልግሎቶችን የማዳረሱ ሥራዎች በጥራታቸውም ሆነ
    በስፋት እየተሻሻሉ በመምጣታቸው በአጠቃላይ ቫይረሱ
    በደማቸው ከሚገኝባቸው ሰዎች መካከል እ.አ.አ.
    በ2018 ብቻ ከአዋቂዎች መካከል 62% ከህጻናት
    መካከል ደግሞ 54% ዕድሜ ልክ በሚወሰደው የጸረ ኤች
    አይ ቪ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ የተቻለ
    ሲሆን ጥረቶቹ ዛሬም እንደ ቀጠሉ ናቸው፡፡
    በመጠቀም ምርመራ የሚያስፈልጋቸውን ተጋላጭ ግለሰቦችን
    ለይቶ ማወቅ፤ከዚያም ማስመርመር
    1.2. ቤት ለቤትና መስክ ላይ የተንቀሳቃሽ የኤች.አይ.ቪ
    ምርመራ አገልግሎት ማካሄድ
    ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ያለባቸውን ሰዎች የትዳር ወይም
    የወሲብ አጋርን ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መለየትና
    ማስመርመር፣
     ኤች.አይ.ቪ እንዳለባቸው በምርመራ የተረጋገጡ ሰዎቸ
    የቲቢ እና የአባለ-ዘር በሽታ ምርመራ እንዲያደርጉ
    ማበረታታትና እንዲመረመሩ ማድረግ ፤
     ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ተጋላጭ ለሆኑ ህጻናት ወይም
    ልጆች የኤች.አይ.ቪ ምርመራ እንዲያደርጉ ማድረግ
     ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸውን ለድጋፍ፣ እንክብካቤና
    ለሕክምና ወደ ጤና ተቋማት መላክ
     በሚታዩቱ የህመም ምልክቶች ላይ በመመርኮዝ የቲቢና
    የአባለ-ዘር በሽታ ተጠርጣሪዎችና ታማሚዎችን መለየትና
    ወደ ጤና ተቋማት በመላክ ማስመርመርና ማሳከም፡፡
    2. 2ኛና 3ኛውን 90 ተግራዊ ለማድረግ ሊሰሩ የሚገቡ
    ሥራዎች
    2ኛና 3ኛውን 90 ተግባራዊ ለማድረግ የማህበረሰብ የኤች.አይ.ቪ
    እንክብካቤና ሕክምና በቀጥታ የሚገኙ አገልግሎቶችን ተግባራዊ
    ማድረግ ሲሆን እነሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
     በአከባቢው ስለሚገኙ የኤች.ኤይ.ቪ መከላከያና
    መቆጣጠሪያ ሥራ አገልግሎቶችን በተመለከተ የህብረተሰቡ
    ግንዛቤ እንዲዳብር ማድረግ፣
     የከፍተኛ ድብርት ተጠቂ የሆኑትን እንዲሁም አደንዛዥ/
    አነቃቂ ለምሳሌ ሲጋራ፤የተለያዩ የሀሺሽ አይነቶችን፤ጫት
    ወዘተ… ተጠቃሚዎችን ፤ መለየትና ከችግሩ እንዲወጡ
    ማገዝ፤ ማበረታታት
     የስነ-ምግብ ዳሰሳ በማካሄድ በምግብ አጠቃቀም ላይ
    ምክክር ማካሄድ
     የንፁሕ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ ምክክር ማካሄድ
     ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ያለባቸው ሰዎች የግል
    እንዲሁም የአከባቢያቸውን ንፅሕና እንዲጠብቁ መርዳትና
    ማበረታታት
     አካባቢያቸው ወባ ያለበት ከሆነ እራሳቸውን ከወባ በሽታ
    እንዲከላከሉ መምከር የመከላከያ ዘዴዎችን የሚማሩበትን
    ሁኔታ ማመቻቸት፡፡
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭነትን ለመቀነስ በሚረዱ ስልቶች ላይ
    ምክክር ማካሄድ
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍልን ማዕከል
    ያደረገ ኮንዶም የማስተዋወቅ ሥራ መሥራትና ኮንዶም
    በማሰራጨት በአግባቡ እንዲጠቀሙ የምክርና የትስስር
    ወይም የቅብብሎሽ አገልግሎት መስጠት
     የፀረ ኤች.አይ.ቪ ህክምና ጥቅም ላይ ግንዛቤ ለማዳበር
    ተጠቃሚውን ማስተማር
     የጸረ ኤች አይ ቪ ህክምና ዘለቄታዊ ቁርኝትን ለማበረታታት
    በተጠቃሚው ፈቃደኝነት ላይ በመመርኮዝ የቤት ለቤት
    ጉብኝት ማካሄድ
     የአቻዎች ደጋፊ ቡድኖችን በተጠቃሚው ቅርበትና ምቾት
    ላይ በመመርኮዝ ማቋቋም፤ በአስፈላጊ ቁሳቁስ ማደራጀትና
    ማጠናከር
     የአቻ ቡድኖች በየጊዜው የውይይት ዕቅድና መድረክ
    እንዲኖራቸው ሁኔታዎችን ማመቻቸት፤ የመወያያ ርዕሶች
    እንዲኖራቸው ማድረግ፤ በውይይት ወቅት ያላግባቡአቸው
    ነጥቦች ላይ በባለሙያ ማብራሪያ እንዲቀርብባቸው
    ሁኔታዎችን ማመቻቸት
     የተጠቃሚው ገቢ እንዲያድግ የአካባቢ/ የመንደር ቁጠባና
    ብድር ቡድኖችን ማቋቋምና ድጋፍ መስጠት ከጥቃቅንና
    አነስተኛ ሥራዎችና ከመሳሰሉት ጋር ማገናኘት
    ይሁን እንጂ የሚሰጡ አገልግሎቶች በቂ ካለመሆናቸው የተነሳ
    ከላይ በተጠቀሰው አመት ብቻ ከአለም ህዝቦች መካከል
    770 ሺህ ሰዎች በዚሁ በሽታና ተያያዥ በሆኑ ችግሮች
    የተነሳ ለህልፈት እንደተዳረጉ መረጃዎች ያሳዩ ሲሆን 1.7
    ሚሊዮን ዜጎች በአዲስ መልክ እንደ ተያዙም ተገምቷል፡፡
    4. በአገራችንም እንደ የኢትዮጵያ ጤና ምርምር እንስቲትዩት
    ትንበያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 ብቻ
    745719 ኤች ኤይ ቪ በደማቸው ያለባቸው ወገኖች
    ሊኖሩ እንደሚቺሉ የተተነበየ ሲሆን በዚሁ አመት 8426
    ሰዎች ከዚሁ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ህይወታቸውን
    ሊያጡ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ 21609
    ሰዎች አዲስ በቫይረሱ እንደሚያዙም ግምቱ ያስረዳል፡፡ ከዚህ
    በተጨማሪ ከፌዴራል ኤች.አይ.ቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ
    ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው በአሁኑ ወቅት
    የኤች.አይ.ቪን ስርጭት 75% መግታት ሲገባን መግታት
    የተቻለው ግን 52% ብቻ ነው፡፡ ቫይረሱ በደማቸው፡፡
    ከላይ ከተጠቀሱት መረጃዎች የምንረዳው ምንም እንኳ
    ኤች.አይ.ቪ ኤድስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ረገድ ከጊዜ ወደ ጊዜ
    መሻሻሎች ቢኖሩም አሁንም በርካታ ሥራዎችን መሠራት እንዳለብን
    ነው፡፡ በተለይም በህብረተሰብ ደረጃ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ
    ስራዎችን መስራት አስፈላጊ ነው፡፡ ህብረተሰቡን ለማሳተፍ ደግሞ
    በጎ ፈቃደኞቸን በመመልመል፤ ማሰልጠንና በማንቀሳቀስ መሠረታዊ
    የኤች.አይ.ቪ መከላከልና መቆጣጠር ሥራን በትኩረት እና ውጤት
    ማምጣት በሚችል መልኩ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ በጎ ፈቃደኞችም
    በአግባቡ ሥራቸውን አውቀው መስራት ያመቻቸው ዘንድ ይህ የበጎ
    ፈቃደኞች ሥንቅ ተብሎ የተሰየመ ጹሁፍ ተዘጋጅቷል፡፡
    ለ/ በኤች.አይ.ቪ መከላከል ሥራ ውስጥ በጎ ፈቃደኛ
    ማን ነው?
    በጎ ፈቃደኛ ማለት በፈቃዱ ያለማንም አስገዳጅነት ጉልበቱን፤
    ጊዜውንና ገንዘቡን በማበርከት በኤች አይ ቪ ወይም በሌላ በሽታ
    የተያዘ ወይም ተያያዥ በሆኑ በሽታዎች ምክንያት የታመሙ ወይም
    ሊታመሙ የሚችሉ ሰዎች ችግሩን እንዲቋቋሙ በተለያየ መንገድ
    ድጋፍ የሚያደርግና የሚያበረታታ ወይም የሚረዳ ግለሰብ ፤ ቡድን
    ወይም ድርጅት ነው፡፡ ድጋፉ የሚሰጠውም በግለሰብ ደረጃ ወይም
    ከድርጅት ጋር በመተባበር ሊሆን ይችላል፡፡
    ሐ/ በጎ ፈቃደኛው ምን ምን እንዲሠራ ይጠበቃል
    የ 90-90-90 ዕቅድን ባለንበት አከባቢ ሁሉ ተግባራዊ እንዲሆን
    መስራት
    90-90-90 ማለት
     የመጀመሪያው 90 ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ውስጥ
    ይኖርባቸዋል ተብለው ከሚገመቱ ሰዎች መካከል 90%
    የሚሆኑ ተመርምረው ውጤታቸውን እንዲያውቁ ማድረግ፤
     2ኛው 90 ኤች.አይ.ቪ በደማቸው እንዳለባቸው
    ከተረጋገጠው ሰዎች መካከል 90% የሚሆኑት የፀረኤች.አይ.ቪ መድኃኒት እንዲወስዱ ማድረግ፤
     የመጨረሻው 90 የፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት
    ከሚወስዱ ሰዎች መካከል 90% የሚሆኑ በደማቸው
    ውስጥ ያለውን የቫይረሱን መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ
    ናቸው፡፡
    1. የመጀመሪያውን 90 ተግባራዊ ለማድረግ
    የሚከተሉን የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም ሥራ መስራት
    1.1. ማህበረሰብ አቀፍ የኤች.አይ.ቪ ምርመራ
    እንዲካሄድ ማድረግ
     በአከባቢው ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉ፣
    ባል ወይም ሚስት የሞተባቸውንና የተፋቱ ባለ ትዳሮችን
    መለየትና በመመዝገብ ወደ ጤና ተቋም በመላክ
    ማስመርመር
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ የሆኑና ቤተሰቦቻቸው በደማቸው
    ውስጥ ኤች.አይ.ቪ ያለባቸውን ህጻናት/ልጆች መለየት
    እና ወደ ጤና ተቋማት መላክና ማስመርመር
     የማህበረሰብ ድጋፍና እንክብካቤ ጥምረትን
    (community Care coalition)
    ማግለልና አድልዎን ለመቀነስ ባህሪ-ተኮር የግንዛቤ
    ማዳበሪያ ሥራዎችን መሥራት
     ለተጎጂዎች የስነልቦናዊ ድጋፍ መሥጠትና
    እንደየእምነታቸው መንፈሳዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ማበረታታት
     ከህክምና ክትትል የጠፉ ታካሚዎችን መፈለግና ወደ
    ህክምና መመለስ እና ደግመው እንዳያቋርጡም በሚገባ
    መምከር፤ ማገዝ፡፡
     በሰውነት ውስጥ ስለሚኖረው ቫይረስ መጠንና ስርጭት
    (CD4 and viral load) ክትትልና ምርመራ
    እንዲያደርጉ ማስተማርና በየጊዜው በፕሮግራም
    እንዲመረመሩ ማድረግ
     ዋና ዋና የጸረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት የጎንዮሽ ጉዳቶችን
    መለየትና ተጠቃሚዎቹ እንዲያውቁት ማድረግ
     የማህበረሰብ የፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ህክምና
    አሰጣጥ ሞዴልን በሚሰጡ መመሪያዎች ላይ በመመርኮዝ
    ተግባራዊ ማድረግ
    መ/ የተሠራውን ሥራ መመዝገብ
    በመጨረሻም የሠራነውን ሥራ መመዝገብና ለሚመለከተው አካል
    ሪፖርት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ እያንዳንዱ አስተባባሪ ድርጅት የራሱ
    የሆነ መረጃ መመዝገቢያና ሪፖርት ማድረጊያ ቅጾች አሉት፡፡ በዚህ
    መልኩ የተሰሩትን ሥራዎች በቅጾቹ መሠረት መዝግቦ ሪፖርት ማድረገ
    ይጠበቃል፡፡
    NEP+
    Tel. +251 116 591 919 / 1818
    P.O. B 789 code 1250
    www.facebook.com/nepplus.nepplus,
    www.nepplus.org, face book Page
    www.facebook.com/Network-of-Networks-of-HIV- Positives-in-Ethiopia

አሁንም ትኩረት ለኤች.አይ.ቪ መከላከል

ጥምረት / TIMRET

የዓለም የኤድስ ቀን በአፋር ክልል በድምቀት ተከበረ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ32ኛ ጊዜ የዓለም ኤድስ ቀን በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ታህሳስ
12 ቀን 2012 ዓ.ም. የኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ክብርት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ
ውሏል፡፡

  1. በጎ አድራጎት ማህበራት በሀገር አቀፍም ሆነ
    በአካባቢ መዋቅር ላይ በፕሮግራም ቀረጻ ፣
    አፈጻጸም. በምዘናና ክትትል ስራ ላይ በመሳተፍ
    ትርጉም ያለው ተሳት እንዲኖራቸው ሁኔታዎችን
    ማመቻቸት
  2. የሀገር ውስጥ ሀብትን ለመጠቀም የሚያስችል
    የአሰራር ስልት መንደፍና ተግባራዊ ማድረግ
    በተለይም ተከማችቶ የሚገኘውን የኤድስ ፈንድ
    ጥቅም ላይ ለማዋል በመንግስት በኩል የህግ
    መሰረት እንዲፈጠር መስራት የሚሉ የወደፊት
    አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ስብሰባው
    ተጠናቋል፡፡
    ቅጽ 6 ቁጥር 1 ጥር 2012 ጥምረት / TIMRET Volume 6 Issue 1 Feb. 2020
    7

    Your ClipBoard is currently empty. Please copy row or element before pasting!

    እጆቼን በሳሙና እታጠባለሁ፣ ርቀቴን እጠብቃለሁ ፣የጸረ-ኤች.አይ.ቪ ሀኪሜን በስልክ አማክራለሁ፡፡ ረጅሙን ጊዜዬን በቤቴ እንዳሳልፍ ሰዎች በሚበዙበት ቦታ አዘውትሬ እንዳልገኝ የጤና ተቋሜ የ6 ካልሆነም የ3 ወር የጸረ-ኤች.አይ.ቪ መድሀኒቴን በአግባቡ ያቅርብልኝ፡፡ በዚህም ኮሮናን እከላከላለሁ፡፡

    
    

    • በአግባቡ የምወስደው የጸረ-ኤች.አይ.ቪ መደሀኒት ኮሮናን ለመከላከል ብርቱ ጋሻ እንደሚሆነኝ መረጃ አግኝቻለሁ፡፡ ዕውቀቱ ለሌላቸው ጓደኞቼ መረጃወን አካፍላለሁ፡፡ ሁላችንም መድሀኒቱን በአግባቡ እየወሰድን የኮሮናን ስጋት እናስወግዳለን፡፡   

    የቦርድ ሰብሳቢ መልክት

    ትኩረት ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝባቸው ማህበራት!!!!

    ኤች.አይቪ/ኤድስ በዓለማችን ብሎም በሀገራችን ላይ ላፉት ሰላሳና አርባ ዓመታት ያህል  በግልና ቤተሰብ እንደዚሁ በማህበረሰብና በሀገር ላይ በጤና ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ላይ አስከፊ ጉዳት ሲያደርስ ቆይቷል፡፡

    መንግስታት ለዚህ ዘርና ቀልም ለማይለየው ወረርሽኝ ምላሽ ለመስጠት  ባደረጉት       ርብርብ  እጅግ    በጣም   ጥሩ የሚባል ውጤት አምጥተው ወረርሽኙን ጥሩ በሚባል ደረጃ  ለመቆጣጠር ተችሎ ነበር፡፡ በዚህ ውጤታማ እንቅስቃሴ ውስጥም ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝባቸው ወገኖች ሰፊ ድርሻ ማበርከታቸው በሁሉም ዘንድ የተመሰከረለት ጉዳይ ነው፡፡

    በተለይ በሀገራች የወረርሽኙን መከሰት ተከትሎ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች በግለሰብ ደረጃ ወደ አደባባይ በመውጣት ትውልድ ይዳን በእኔ ይብቃ በሚል መርህ የምስክርነታቸውን  ቃል  ሠጥተው  ዜጎች ራሳቸውን ከወረርሽኙ እንዲጠብቁ  አድርገዋል፡፡

    እነዚህ ኤድስ ላይ የዘመቱ ጀግኖች የችግሩን ስፋት በመገንዘብ ከተበታተነ ይልቅ ባንድ ያበረ ድምጽ  ለውጥ  እንደሚያመጣ  ተረድተው ራሳቸውን በማህበር በማዋቀር ወረርሽኙን ሲዋጉ ቆይተው ማህበራት ክልላዊ ጥምረቶችንና ብሄራዊ  ጥምረትን  ፈጥረው  ማህበረሰቡን ከኤድስ ሲታደጉና ለራሳቸውም መብት ሲታገሉም ቆይተዋል፡፡ ለዚህ ስራ መሳካትም ድጋፍ ሲያደርጉልን የቆዩትን የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ቫይረሱ በደማቸው በሚገኝባቸውና ባንድ ወቅት ማህበረሰቡን ሲያስተምሩ ለነበሩና አሁን በህይወት በሌሉ ጀግኖች የማህበር አባሎቻችን ስም ሳላመሰግን አላልፍም፡፡

    ማህበራትና ጥምረቶች ወረርሽኙን  ከመንግስት ጎን ቆመው ከመከላከልና ከመቆ ጣጠር ባሻገር በቫይረሱ ምክንያት እቤት የዋሉ አቅመ ደካሞችንና በዚሁ በሽታ ወላጆቻቸውን ያጡ ችግረኛ ህጻናት የጤናና የኢኮኖሚ ድጋፍ  የሚያገኙበትን የግልና ተቋማዊ የገቢ ማስገኛ ዘዴዎችን በመፍጠር የእለት ጉርስ እንዲያገኙና ልጆች ትምህርት ቤት መሄድ እንዲችሉ አድርገዋል፡፡

    ሆኖም እነዚህ ማህበራት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ በመጣው የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ ምክንያት በርካታ አባሎቻቸው ከእይታ እየጠፉና የማህበራቱም ንቁ ተሳትፎ እየደበዘዘ መጥቷል፡፡

    አሁን እንደ አዲስ እያገረሸ የመጣውን የኤች.አይ.ቪ ስርጭት እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በጋራ በተቀናጀ መንገድ ለመመከት የእነዚህ ማህበራት መጠናከር ወሳኝ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ስለሆነም አሁን ላይ በተበጣጠሰ መልኩ በተለያዩ ክልሎች እየተመደበ ያለው የሁለት በመቶ የኤድስ በጀት ወጥነትና ዘለቄታን በተላበሰ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ ማህበራት ተጠናክረው ወረርሽኙን በመግታትም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬን የሚሰጧቸው የተለያዩ ድጋፎች እንዲያገኙ በማድረግ ዳግም ማህበራቱ ወደ ንቁ እንቅስቃሴያቸው የሚመጡበት መንገድ እንዲመቻች የፌደራልንም ሆነ የክልል መንግስታትን በአንክሮ እንጠይቃለን፡፡

    መልካም ንባብ

    ኮቪድ19 እና ኤች.አይ.ቪ.(HIV)

    ዶ/ር ብሩክ አለማየሁ (የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት)

    በአለማችን ከ38ሚሊየን የሚበልጥ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ኤች.አይ.ቪ.(HIV) በደማቸው ውስጥ ይኖራሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ ሁለት ሶስተኛው የሚገኙት በአህጉራችን አፍሪካ ሲሆን የሀገራችንም ሁኔታ ብዙም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ በኢትየጵያ ከ4 ወራት በፊት እንደተገለፀው በቫይረሱ እየተያዙ ያሉ አዳዲስ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደሚገኝና ከሶስት ክልሎች ውጪ በቀሩት የአገሪቱ ክፍሎች በወረርሽኝ ደረጃ ይገኛል፡፡


    ከሰሞነኛው የኮቪድ19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የኤች.አይ.ቪ ታካሚዎቻችን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክረናል፡፡

    ጥያቄዎቻቸውና መልሶቹ እንደሚከተለው ቀርበዋል

    ጥያቄ 1 ፡- ኤች.አይ.ቪ. (HIV) በደሜ ውስጥ እንዳለ ተነግሮኛል:: ነገር ግን መድሃኒት አልጀመርኩም፡፡ ምን ላድርግ?

    መልስ፡– ከዚህ በፊትም ይሁን በአሁኑ ወቅት HIV በደማቸው እንዳለባቸው ተነገሯቸው የህክምና ክትትል ወይም መድሃኒት ያልጀመሩ ታካሚዎች በቶሎ ሀኪም አንዲያማክሩና እና ልዩ ምክንያት ወይም ሕክምና እንዳይጀምሩ የሚከለክል የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር የፀረ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) መድሃኒቶችን እንዲጀምሩ ይመከራል፡፡

    ከኮቪድ አንፃር ልዩ መረጃ ባይኖርም አነዚህን መድኃኒቶች መጀመር የሰውነት የመከላከል አቅም እንዲጎለብትና ሰውነታችን ለተለያዩ ተጓዳኝ ኢንፌክሽኖች እንዳይጋለጥ ይረዳል፡፡ የፀረ ኤች.አይ.ቪ. መድሃኒት የሲደ4 (CD4) ቁጥር አነሰም በዛም በየትኛውም ደረጃ መጀመር አለበት፡፡

    ጥያቄ 2. በኤች.አይ.ቪ. (HIV) የተያዙ ሰዎች በኮቪድ19 የመያዝ እድላቸው ከሌላው አንፃር የበለጠ ነው?

    ባጠቃላይ መድሃኒት ያልጀመሩ፣ ሲዲ4(CD4) ቁጥራቸው ዝቅተኛ የሆነ እና በደማቸው ያለው የቫይረስ መጠን (Viral Load) ከፍተኛ የሆኑ የኤች.አይ.ቪ. ታካሚዎች ለሌሎች ኢንፌክሽኖች የበለጠ ተጋላጭ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም እድሜያቸው የገፋና ተደራራቢ ህመም ያለባቸው ሰዎች በኮቪድ19 ከተያዙ ጠንከር ባለ ሁኔታ ሊታመሙ የሚችሉበት እድል ሰፊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን እስካሁን ድረስ ኤች.አይ.ቪ. እና ኮቪድ19 መሀከል ያለውን መስተጋብር ያሳየ ልዩ መረጃ የለም፡፡

    በተለይም መድሃኒት እየወሰዱ ያሉና ጥሩ ቁጥጥር ላይ ያሉ ታካሚዎች ከጤነኛ ሰው የተለየ ተጋላጭነት አላቸው ተብሎ አይታሰብም፡፡ ይሁንና ያለው መረጃ በቂ ካለመሆኑ አንፃር እና ከዚህ በፊት የተከሰቱ መሰል ወረርሽኞች ካደረሱት አደጋ አንፃር ታማሚዎች በቂ ጥንቃቄዎችን ማድረግ አለባቸው፡፡

    የመረጃ ውስንነቱ እንዳለ ሆኖ በተለይ ሲዲ4(CD4) ቁጥራቸው ዝቅተኛ የሆነ እና በደማቸው ያለው የቫይረስ መጠን (Viral Load) ከፍተኛ የሆኑ ታካሚዎች ለጠና ህመም የተጋለጡ ናቸው ተብሎ ይታሰባል፡፡

    ከኤች.አይ.ቪ በተጨማሪም የታካሚው እድሜና ሌሎች ቋሚ ህመሞችም ተጨማሪ ሚና እንደሚኖራቸው መረሳት የለበትም፡፡

    ጥያቄ 3. የ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) ታካሚዎች ራሳቸውን ከኮቪድ 19 ለመከላከል ምን ማድረግ አለባቸው?

    ባሁኑ ሰዓት ኮቪድ19 ክትባት የለውም፡፡ ብቸኛው የመከላከያ መንገድ በቫይረሱ ላለመያዝ እራስን መጠበቅ ነው፡፡ ይህንንም ለማድረግ መደበኞቹን የመከላከያ መንገዶች በአግባቡ መተግበር ለሁሉም የኤች.አይ.ቪ. (HIV) ታካሚዎች ይመከራል፡፡ እነዚህም፡-

    • ሳል፣ ትኩሳት እና ጉንፋን መሰል ህመም ካላቸው ሰዎች መራቅ
    • በአግባቡና በተደጋጋሚ እጅን መታጠብ/በአልኮል ማፅዳት
    • ባልታጠበ እጅ አፍ፣ አፍንጫ ወይም ዓይንን አለመንካት
    • ሰዎች በሚሰበሰቡባቸው ቦታዎች አለመገኘት
    • አላስፈላጊ ጉዞዎችንና እንቅስቃሴዎችን ማስቀረት
    • ከዚህም በተጨማሪ
    • የተመጣጠነ ምግብ መመገብ
    • በቂ እንቅልፍ/እረፍት ማግኘት
    • በተቻለ መጠን ውጥረትን መቀነስ
    • መድኃኒት ሳይረሱና ሰዓት ሳያሳስቱ በየዕለቱ መዋጥ
    • ለወራት የሚያቆይ በቂ መድኃኒት እጅ ላይ መያዝ
    • ልዩ ስሜት/ችግር ካለ ከሀኪም ጋር መመካከር

    ጥያቄ 4. የ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) ታካሚ ነኝ፡፡ ሁልጊዜ ማስክ ማድረግ አለብኝ ወይ?

    ማስክ ማን ያድርግ ማን አያድርግ የሚለው ነገር ብዙ ግርታ ያለው ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ እየወጡ ያሉ መረጃዎችን ተከትሎ ማንኛውም ሰው ከቤት ሲወጣ በተለይም ደግሞ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ በማይችልበት ሁኔታ ላይ ማስክ ቢያደርግ መልካም ነው፡፡ ይህ ምክረ ሀሳብ በሁሉም የኤች.አይ.ቪ. ታካሚዎችም ቢተገበር የተሻለ ነው፡፡

    ጥያቄ 5. የ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) ታካሚ ነኝ፡፡ በኮቪድ19 እንደተያዝኩ እጠረጥራለሁ፡፡ ምን ማድረግ አለብኝ?

    አንድ ሰው የኮቪድ 19 ምልክቶች ከታዩበት በተቻለ መጠን በቶሎ ከሀኪሙ ጋር (በስልክና በአመቺ መንገድ) ሊመካከር ይገባዋል፡፡ ከዚያ በተጨማሪ ግን  የኮቪድ19 ምልክቶች ከታዩበት ሊያደርጋቸው የሚገቡ ጥንቃቆዎችና ሂደቶች በሚገባ ተግባራዊ ማድረግ ይጠቅማል፡፡

    ጥያቄ 6. የፀረ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) መድሃኒቶች ኮቪድ19ን ለማከም ይጠቅማሉ?

    አንዳንድ የፀረ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) መድሃኒቶች ኮቪድን ለማከም ጥናት እየተደረገባቸው እንደሆነ ተነስቷል፡፡

    ከዚህ አንፃር በተለይ የሚነሳው ካሌትራ [Kaletra(Lopinavir boosted with Ritonavir (LPV/r))] ነው፡፡ መጀመሪያ ላይ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው ተብሎለት የነበረ ቢሆንም ከቻይና በወጡ አንዳንድ ጥናቶች መሰረት ግን የተጠበቀውን ያህል ውጤት አላሳየም፡፡ ይሄ እና ሌሎች የኤች.አይ.ቪ መድሃኒቶች ላይ ከ15 በላይ ጥናቶች እየተካሄዱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ውጤቶቹን መጠበቅ መልካም ነው፡፡

    ጥያቄ7. በኮቪድ19 እንዳልያዝ የሚከላከልልኝ የፀረ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) መድሃኒት አለ? የምወስደው መድሃኒት ሌላ ከሆነስ መድሃኒቴን ማስቀየር ይጠቅመኛል?

    ኮቪድ19ን ይከላከላል በሚል መድሃኒታቸውን ወደ ካሌትራ ለማስቀየር ጥያቄ የሚያቀርቡ ታካሚዎች ብዙም ባይሆኑም አሉ፡፡ ይህንን በተመለከተም ያለው ጥናት አጅግ ደካማ ነው፡፡

    በተለይ ካሌትራ ካሉት የጎንዮሽ ችግሮች አንፃር ኮቪድ19ን ለመከላከል ከሚል ሃሳብ ብቻ ተነስቶ መድሃኒትን ወደ እሱ ማስቀየር በፍፁም አይመከርም፡፡

    ጥያቄ8. ሀገራት የፀረ ኤች.አይ.ቪ. (HIV) መድሃኒቶችን ኮቪድ19ን ለማከም ከተጠቀሙ እጥረት ሊከሰት አይችልም ወይ?

    አሁን ባለንበት ሁኔታ ይህ ትልቅ ስጋት ነው ተብሎ አይታሰብም፡፡ ምክንያቱም ካሌትራን በስፋት ለኮቪድ19 እየተጠቀምንበት ስላልሆነ እና ካሌትራን የሚጠቀሙ የኤች.አይ.ቪ. ታካሚዎች ጥቂት በመሆናቸው ነው፡፡

    ይሁንና ብዙ የኮቪድ19 ታካሚዎችን በእዚህ እና ሌሎች ፀረ ኤች.አይ.ቪ. መድሃኒቶች ማከም የምንጀምር ከሆነ የመድሃኒት እጥረት ሊከሰት የሚችልበት እድል አለ፡፡ ስለዚህም ሀገራት ይህንን ጉዳይ በቅርበት ሊከታተሉ እና እጥረት እንዳይከሰት የተለያዩ አማራጮችን መጠቀም ይኖርባቸዋል፡፡

    የጤና ወግ

    167 case managers take refreshment training

    167 case managers, working in the Oromoia region health facilities took ART case management refreshment training for four consecutive days in Adama town.

    The training incorporated the new ART drug features that began for use to PLHIVs in the previous six months, told during the training closing remark. 

    The closing remark was made in the presence of NEP+ Board Chairman, Ato Edilam G/silasse. Before he forwarded his closing speech, the trainees’ representatives explained their challenges that faced them while they were on duty.

    The representatives explained that they are often in difficulty while they record clients’ profile as they use different log book format that came from different partners. The dissimilarity of CDC’s and other partners log book was mentioned by the trainees. 

    The trainees have also disclosed their complain that the discrimination by some health facilities’ administrations. According to them some health facility administrators do not consider case managers equally with other health facilities’ staff. Due to this malfunctions case manager do not get gown, hygiene materials like soap and soft papers.

    The case managers have also put forwarded other salary and benefit related administration problems to the high level NEP+ officials.

    Ato Edilam G/silasse , NEP+ Board Chairman, after the complaint presentation appreciating the case managers as they still working under these all pressure with their great endurance. “This shows that you are committed to save others live,” Ato Edlam said. “The survival of you (case managers) means the survival of hundred thousands of PLHIVs “ Ato Edilam added.

    Ato Edilam G/silasse

    NEP+ Board Chairman

    He also assured them that all the problem mentioned by the trainees will be solved step by step.

    Earlier to Ato Edlam, NEP+ Executive Director Ato Mekonnen Alem also assured the case managers that NEP+ has always strived for their healthy working environment. He also said that so far some discussions were also held with regional health bureaus officials to avoid malfunctions occurred in the health facilities against case managers. “This trend will be also continued in 2020 planning year with full enthusiasm,” Ato Mekonnen assured the case managers.

    Ato Mekonnen Alemu

    NEP+ Executive Director

    Ato Diku worku , NEP+ Program Manager, on his behalf said regarding log book dissimilarity NEP+ will hold a discussion with all government and non government actors to keep the uniformity of the log sheets.

    Ato Dinku Worku

    NEP+ Program Manager

    He also underlined similar refreshment training is important in a yearly base as it enables the case managers to have up to date knowledge about what they are doing. As a result of this case managers can provide comprehensive and effective service to their clients, Ato Dinku added.

    ኔፕ ፕላስ ከኤች አይ ቪ መከላከያና መቆጣጠሩ ስራ በተጨማሪ በጤና እና ሌሎች የልማት ስራዎች ላይ ለመሰማራት በዝግጂት ላይ መሆኑን አስታወቀ፤

    ሰኞ ጥር 25 ቀን 2012 አድስ አበባ

     ኔፕ ፕላስ ከተሰማራበት የስራ ዘርፎች በተጨማሪ በሌሎች  የስራ መስኮች ለመሰማራት እንደሚፈልግ ገልጸ፡፡ ይህንን የገለጹት የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ መኮንን አለሙ ሲሆኑ በአዳማ ከተማ በተካሄደው ከጥር 23-24 2012 እንደ አውሮፕያዊያን አቆጣጠር የ2020 እቅድ ውይይት ላይ ነው፡፡ እንደ ስራ አስኪያጁ ገለጻ ድርጅቱ እ.ኤ.አ ከ 2020 ጀምሮ ከኤች.ኤይ.ቪ መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች በተጨማሪ በሌሎች ተላላፊና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች መከላከል፤ ሌሎች የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ፤ በልማት፤ በዴሞክራሲ ግንባታና ሰብአዊ መብት አጠባበቅ ስራዎች ላይ ለማሰማራት የሚያስችሉ ቅድሚያ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ እነዚህ ሥራዎችን ለማከናወንም የቴክኒክና የገንዘብ ድጋፍ ከእክስፐርቲዝ ፍራንስ / Expertize France/ ከተባለ አለም አቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ቃል እንደተገባለት በዚሁ ጊዜ ተብራርቷል፡፡

    ድርጅቱ በአባላት አቅም ግንባታ፤ በሃብት ማበልጸግ ስራዎች፤ ኤች አይ ቪ በደማቸው ላለባቸው ግለሰቦች ድምጽ ሆኖ የማገልገል ስራዎችን  አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጾአል ፡፡

    ዕቅዶቹን ለማሳካት የሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ያለሆኑ ድርጅቶች ሁሉ እንደተለመደው ከጎኑ እንዲቆሙ ሰራተኛውም በሙሉ  በጋራ መነቃቃት እና በቁርጠኝነት አለማዎቹን   ለማሳከት  ጥረት እንዲያደርግ ጥሪአቸውን አስተላልፈዋል፡፡

    በጌታቸው ጎንፋ

    Ato Mekonnen Alemu Executive Director

    NEP+ is to revise its Thematic Areas

    February 03 / 2020, Addis Ababa

    NEP+ Executive Director, Ato Mekonnin Alemu, in his speech at NEP+ 2020 planning meeting conducted from Feb 02-3 2020 at Adama Town Comfort Hotel, disclosed that Network of Networks of HIV Positives in Ethiopia (NEP+) is going to revise its Mission, Vision and all its thematic areas soon. According to the director, NEP+ will include other health-related provisions, developmental programs, human rights protection, and democratization related activities into its current HIV/AIDS prevention and control activities starting from 2020 budget year.

    In his speech, the director also disclosed that the organization has got a promise from Expertise France for technical and financial support for the revision and related activities.

    In his speech, the director also stressed that NEP+ will continue to serve the PLHIV communities through capacity building, resource mobilization & allocation and relaying the voice PLHIVs. During this speech, the director called upon all stakeholders including the staff of the organization to continue their usual support and commitment to materialize all the missions and objectives of the organization.

    By Getachew

    ኔፕ ፕላስ ለ2020 የባጀት አመት ለኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ሥራ  ከ195 ሚሊዮን ብር በበጀት በመደበ ዕቅድ አዘጋጀ

    ሰኞ ጥር 25 ቀን 2012 አድስ አበባ

    ኔፕ ፕላስ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 ዓ.ም ተግባራዊ የሚያደርጋቸውን ረቂቅ ዕቅድ ማዘጋቱን አስታወቀ፡፡ የድርጅቱ የክትትልና ምዘና መምሪያ ሓላፊ አቶ በላይ ረታ እንዳብራሩት ዕቅዱ በእያንዳንዱ መምሪያ ከተዘጋጀና በአንድ ላይ ከተደራጀ ቦኃላ የበለጠ እንድያዳብሩት ለመላው የድርጅቱ ሠራተኞች ከጥር 23-24 2012 ለ2 ቀናት በአዳማ ከተማ ቀርቦ እንደ ተወያዩበትና እንድያዳብሩት  ተደርገዋል ብለዋል፡፡

    በቅዕዱም በጤና ተቋማት የሚፈጸሙ የጸረ ኤች አይ ቪ ህክምና እና ቁርኝት ሥራዎች እንድሁም በማህበረሰብ ውስጥ የኤች አይቪ መከላከልና መቐጣጠር ሥራዎች ትኩረት ተሰጥተዋቸዋል ብሏል፡፡ዕቅዱ ሲዘጋጅም የመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎች፡ የድርጅቱ የ5 አመት መርህ ዕቅድ፡ ያለፈው ዓመት የድርጅቱ የስራ አፈጻጻም እንድሁም የወደ ፊቱ የድርጅቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ከግምት መግባታቸው ተብርርቷል፡፡ ከዘህ በተጨማሪ ድርጅቱ ከለጋሾች ጋር በተለይም ከግሎባል ፈንድና ከአሜርካ የበሽታ መከላከያ ማዕከል(CDC) የተፈራረማቸውና ስምምነት የተገባበቸው ፕሮጀክቶች እና ወደ ፊት የሚበለጽጉ ሀብቶች ከግምት በማስገበት መሆኑን መምሪያ ኃላፊው ጨምሮ አበራርቷል፡፡

    ድርጅቱ በበጀት አመቱ በአጠቃላይ ከ195 ሚሊዮን ብር በላይ የመደበ ቢሆንም ለሥረው ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆና ስራዎቹም በዘጠኙም ክልሎችና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች ተግባራዊ እንደሚሆኑ ተብራርቷል፡፡በመጨረሻም በድርጅቱ መመሪያ መሠረት ረቂቅ ዕቅዱ ለድርጅቱ ቦርድና ጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ አስፈላጊው ግበአት ተጨምሮበት እንደሚጸድቅ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

    በጌታቸው ጎንፋ

    NEP+ has allocated over 195 million birr for HIV/AIDS prevention and Control activities for 2020 budget year

    February 03 / 2020, Addis Ababa

    Network of Networks of HIV Positives in Ethiopia (NEP+) in its planning meeting conducted from Feb 02-3 2029 at Adama Town Comfort Hotel disclosed that it has allocated over 195 million Birr for HIV/AIDS prevention and control activities for the 2020 budget year. According to Ato Belay Reta, NEP+ Monitoring and Evaluation Department manager, the existing 6 departments has drafted their own plan and this plan has been compiled and discussed up on by the whole staff for two days at Adama Town Comfort Hotel to be enriched.

    According to Ato Belay, in the plan, activities that are going to be implemented in health facilities on adherence to treatment (activities that are supported by CDC) and activities that are implemented in the community on HIV prevention and control programs (that are supported by global fund) has been mainly focused on. The manager added, in addition to projects that the organization has entered in to agreement with donors, resources that is going to be mobilized from different sources has been taken in to account.

    For the budget year, the organization has allocated over 195 million Birr which is not enough for what the organization needs and the allocated budget is going to be implemented in 9 regional states and two city administrations. According to NEP+ regulation the plan is going to be endorsed by the Board of Directors and approved by the general Assembly. By

    Getachew Gonfa

    « of 3 »

    About NEP

    The NEP+, formerly known as AELWHA (Association of Ethiopians Living with HIV/AIDS), is established in October 2004 to raise and relay the collective voice of people living with HIV.

    GPS Location of NEP+ Office

    Contact Us

    Address: Mexico Chamber of Commerce building 5th floor.
    Phone: +251 111 659 1414/1818/1919
    Fax: +251 111 659 1010
    P.O.Box: 780 Code-1250
    Email: eshetu@nepplus.org / aelwha@ethionet.et