ኔትዎርክ ኦፍ ኔትዎርክስ ኦፍ ኤች
አይቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ
(ኔፕፕላስ)

  • ኤች.አይ.ቪ ኤድስን ለመከላከልና
    ለመቆጣጠር የበጎ ፈቃደኞች ስንቅ
    ሀ/ መግቢያ
    ኤች.አይ.ቪ ኤድስ በአለም ላይ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የበርካታ
    ሰዎችን ህይወት ከመቅጠፉም በተጨማሪ ዛሬም ድረስ በርካታ ዜጎች
    ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅትም
    የሚከተሉት እውነታዎች ይስተዋላሉ፡፤
    1. ይህ ወረርሽኝ አሁንም በአለም ላይ ዋንኛ የጤና ችግር
    ሲሆን ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እንደ እ.አ.አ ዲሴምበር
    2018 መጨረሻ ድረስ ከ32 ሚሊዮን ህዝብ በላይ
    ህይወት እንደሳጣ እና ከ37.9 ሚሊዮን ህዝብ በላይ
    ደግሞ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡
    2. በአለም አቀፍ ደረጃ በተሰጠው ትኩረት ምክንያት
    በሽታውን የመከላከሉና የመቆጣጠሩ ስራ እንዲሁም
    አገልግሎቶችን የማዳረሱ ሥራዎች በጥራታቸውም ሆነ
    በስፋት እየተሻሻሉ በመምጣታቸው በአጠቃላይ ቫይረሱ
    በደማቸው ከሚገኝባቸው ሰዎች መካከል እ.አ.አ.
    በ2018 ብቻ ከአዋቂዎች መካከል 62% ከህጻናት
    መካከል ደግሞ 54% ዕድሜ ልክ በሚወሰደው የጸረ ኤች
    አይ ቪ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ የተቻለ
    ሲሆን ጥረቶቹ ዛሬም እንደ ቀጠሉ ናቸው፡፡
    በመጠቀም ምርመራ የሚያስፈልጋቸውን ተጋላጭ ግለሰቦችን
    ለይቶ ማወቅ፤ከዚያም ማስመርመር
    1.2. ቤት ለቤትና መስክ ላይ የተንቀሳቃሽ የኤች.አይ.ቪ
    ምርመራ አገልግሎት ማካሄድ
    ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ያለባቸውን ሰዎች የትዳር ወይም
    የወሲብ አጋርን ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መለየትና
    ማስመርመር፣
     ኤች.አይ.ቪ እንዳለባቸው በምርመራ የተረጋገጡ ሰዎቸ
    የቲቢ እና የአባለ-ዘር በሽታ ምርመራ እንዲያደርጉ
    ማበረታታትና እንዲመረመሩ ማድረግ ፤
     ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ተጋላጭ ለሆኑ ህጻናት ወይም
    ልጆች የኤች.አይ.ቪ ምርመራ እንዲያደርጉ ማድረግ
     ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸውን ለድጋፍ፣ እንክብካቤና
    ለሕክምና ወደ ጤና ተቋማት መላክ
     በሚታዩቱ የህመም ምልክቶች ላይ በመመርኮዝ የቲቢና
    የአባለ-ዘር በሽታ ተጠርጣሪዎችና ታማሚዎችን መለየትና
    ወደ ጤና ተቋማት በመላክ ማስመርመርና ማሳከም፡፡
    2. 2ኛና 3ኛውን 90 ተግራዊ ለማድረግ ሊሰሩ የሚገቡ
    ሥራዎች
    2ኛና 3ኛውን 90 ተግባራዊ ለማድረግ የማህበረሰብ የኤች.አይ.ቪ
    እንክብካቤና ሕክምና በቀጥታ የሚገኙ አገልግሎቶችን ተግባራዊ
    ማድረግ ሲሆን እነሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
     በአከባቢው ስለሚገኙ የኤች.ኤይ.ቪ መከላከያና
    መቆጣጠሪያ ሥራ አገልግሎቶችን በተመለከተ የህብረተሰቡ
    ግንዛቤ እንዲዳብር ማድረግ፣
     የከፍተኛ ድብርት ተጠቂ የሆኑትን እንዲሁም አደንዛዥ/
    አነቃቂ ለምሳሌ ሲጋራ፤የተለያዩ የሀሺሽ አይነቶችን፤ጫት
    ወዘተ… ተጠቃሚዎችን ፤ መለየትና ከችግሩ እንዲወጡ
    ማገዝ፤ ማበረታታት
     የስነ-ምግብ ዳሰሳ በማካሄድ በምግብ አጠቃቀም ላይ
    ምክክር ማካሄድ
     የንፁሕ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ ምክክር ማካሄድ
     ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ያለባቸው ሰዎች የግል
    እንዲሁም የአከባቢያቸውን ንፅሕና እንዲጠብቁ መርዳትና
    ማበረታታት
     አካባቢያቸው ወባ ያለበት ከሆነ እራሳቸውን ከወባ በሽታ
    እንዲከላከሉ መምከር የመከላከያ ዘዴዎችን የሚማሩበትን
    ሁኔታ ማመቻቸት፡፡
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭነትን ለመቀነስ በሚረዱ ስልቶች ላይ
    ምክክር ማካሄድ
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍልን ማዕከል
    ያደረገ ኮንዶም የማስተዋወቅ ሥራ መሥራትና ኮንዶም
    በማሰራጨት በአግባቡ እንዲጠቀሙ የምክርና የትስስር
    ወይም የቅብብሎሽ አገልግሎት መስጠት
     የፀረ ኤች.አይ.ቪ ህክምና ጥቅም ላይ ግንዛቤ ለማዳበር
    ተጠቃሚውን ማስተማር
     የጸረ ኤች አይ ቪ ህክምና ዘለቄታዊ ቁርኝትን ለማበረታታት
    በተጠቃሚው ፈቃደኝነት ላይ በመመርኮዝ የቤት ለቤት
    ጉብኝት ማካሄድ
     የአቻዎች ደጋፊ ቡድኖችን በተጠቃሚው ቅርበትና ምቾት
    ላይ በመመርኮዝ ማቋቋም፤ በአስፈላጊ ቁሳቁስ ማደራጀትና
    ማጠናከር
     የአቻ ቡድኖች በየጊዜው የውይይት ዕቅድና መድረክ
    እንዲኖራቸው ሁኔታዎችን ማመቻቸት፤ የመወያያ ርዕሶች
    እንዲኖራቸው ማድረግ፤ በውይይት ወቅት ያላግባቡአቸው
    ነጥቦች ላይ በባለሙያ ማብራሪያ እንዲቀርብባቸው
    ሁኔታዎችን ማመቻቸት
     የተጠቃሚው ገቢ እንዲያድግ የአካባቢ/ የመንደር ቁጠባና
    ብድር ቡድኖችን ማቋቋምና ድጋፍ መስጠት ከጥቃቅንና
    አነስተኛ ሥራዎችና ከመሳሰሉት ጋር ማገናኘት
    ይሁን እንጂ የሚሰጡ አገልግሎቶች በቂ ካለመሆናቸው የተነሳ
    ከላይ በተጠቀሰው አመት ብቻ ከአለም ህዝቦች መካከል
    770 ሺህ ሰዎች በዚሁ በሽታና ተያያዥ በሆኑ ችግሮች
    የተነሳ ለህልፈት እንደተዳረጉ መረጃዎች ያሳዩ ሲሆን 1.7
    ሚሊዮን ዜጎች በአዲስ መልክ እንደ ተያዙም ተገምቷል፡፡
    4. በአገራችንም እንደ የኢትዮጵያ ጤና ምርምር እንስቲትዩት
    ትንበያ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2020 ብቻ
    745719 ኤች ኤይ ቪ በደማቸው ያለባቸው ወገኖች
    ሊኖሩ እንደሚቺሉ የተተነበየ ሲሆን በዚሁ አመት 8426
    ሰዎች ከዚሁ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ህይወታቸውን
    ሊያጡ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ 21609
    ሰዎች አዲስ በቫይረሱ እንደሚያዙም ግምቱ ያስረዳል፡፡ ከዚህ
    በተጨማሪ ከፌዴራል ኤች.አይ.ቪ መከላከያና መቆጣጠሪያ
    ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው በአሁኑ ወቅት
    የኤች.አይ.ቪን ስርጭት 75% መግታት ሲገባን መግታት
    የተቻለው ግን 52% ብቻ ነው፡፡ ቫይረሱ በደማቸው፡፡
    ከላይ ከተጠቀሱት መረጃዎች የምንረዳው ምንም እንኳ
    ኤች.አይ.ቪ ኤድስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ረገድ ከጊዜ ወደ ጊዜ
    መሻሻሎች ቢኖሩም አሁንም በርካታ ሥራዎችን መሠራት እንዳለብን
    ነው፡፡ በተለይም በህብረተሰብ ደረጃ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ
    ስራዎችን መስራት አስፈላጊ ነው፡፡ ህብረተሰቡን ለማሳተፍ ደግሞ
    በጎ ፈቃደኞቸን በመመልመል፤ ማሰልጠንና በማንቀሳቀስ መሠረታዊ
    የኤች.አይ.ቪ መከላከልና መቆጣጠር ሥራን በትኩረት እና ውጤት
    ማምጣት በሚችል መልኩ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ በጎ ፈቃደኞችም
    በአግባቡ ሥራቸውን አውቀው መስራት ያመቻቸው ዘንድ ይህ የበጎ
    ፈቃደኞች ሥንቅ ተብሎ የተሰየመ ጹሁፍ ተዘጋጅቷል፡፡
    ለ/ በኤች.አይ.ቪ መከላከል ሥራ ውስጥ በጎ ፈቃደኛ
    ማን ነው?
    በጎ ፈቃደኛ ማለት በፈቃዱ ያለማንም አስገዳጅነት ጉልበቱን፤
    ጊዜውንና ገንዘቡን በማበርከት በኤች አይ ቪ ወይም በሌላ በሽታ
    የተያዘ ወይም ተያያዥ በሆኑ በሽታዎች ምክንያት የታመሙ ወይም
    ሊታመሙ የሚችሉ ሰዎች ችግሩን እንዲቋቋሙ በተለያየ መንገድ
    ድጋፍ የሚያደርግና የሚያበረታታ ወይም የሚረዳ ግለሰብ ፤ ቡድን
    ወይም ድርጅት ነው፡፡ ድጋፉ የሚሰጠውም በግለሰብ ደረጃ ወይም
    ከድርጅት ጋር በመተባበር ሊሆን ይችላል፡፡
    ሐ/ በጎ ፈቃደኛው ምን ምን እንዲሠራ ይጠበቃል
    የ 90-90-90 ዕቅድን ባለንበት አከባቢ ሁሉ ተግባራዊ እንዲሆን
    መስራት
    90-90-90 ማለት
     የመጀመሪያው 90 ኤች.አይ.ቪ በደማቸው ውስጥ
    ይኖርባቸዋል ተብለው ከሚገመቱ ሰዎች መካከል 90%
    የሚሆኑ ተመርምረው ውጤታቸውን እንዲያውቁ ማድረግ፤
     2ኛው 90 ኤች.አይ.ቪ በደማቸው እንዳለባቸው
    ከተረጋገጠው ሰዎች መካከል 90% የሚሆኑት የፀረኤች.አይ.ቪ መድኃኒት እንዲወስዱ ማድረግ፤
     የመጨረሻው 90 የፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት
    ከሚወስዱ ሰዎች መካከል 90% የሚሆኑ በደማቸው
    ውስጥ ያለውን የቫይረሱን መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ
    ናቸው፡፡
    1. የመጀመሪያውን 90 ተግባራዊ ለማድረግ
    የሚከተሉን የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም ሥራ መስራት
    1.1. ማህበረሰብ አቀፍ የኤች.አይ.ቪ ምርመራ
    እንዲካሄድ ማድረግ
     በአከባቢው ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉ፣
    ባል ወይም ሚስት የሞተባቸውንና የተፋቱ ባለ ትዳሮችን
    መለየትና በመመዝገብ ወደ ጤና ተቋም በመላክ
    ማስመርመር
     ለኤች አይ ቪ ተጋላጭ የሆኑና ቤተሰቦቻቸው በደማቸው
    ውስጥ ኤች.አይ.ቪ ያለባቸውን ህጻናት/ልጆች መለየት
    እና ወደ ጤና ተቋማት መላክና ማስመርመር
     የማህበረሰብ ድጋፍና እንክብካቤ ጥምረትን
    (community Care coalition)
    ማግለልና አድልዎን ለመቀነስ ባህሪ-ተኮር የግንዛቤ
    ማዳበሪያ ሥራዎችን መሥራት
     ለተጎጂዎች የስነልቦናዊ ድጋፍ መሥጠትና
    እንደየእምነታቸው መንፈሳዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ማበረታታት
     ከህክምና ክትትል የጠፉ ታካሚዎችን መፈለግና ወደ
    ህክምና መመለስ እና ደግመው እንዳያቋርጡም በሚገባ
    መምከር፤ ማገዝ፡፡
     በሰውነት ውስጥ ስለሚኖረው ቫይረስ መጠንና ስርጭት
    (CD4 and viral load) ክትትልና ምርመራ
    እንዲያደርጉ ማስተማርና በየጊዜው በፕሮግራም
    እንዲመረመሩ ማድረግ
     ዋና ዋና የጸረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት የጎንዮሽ ጉዳቶችን
    መለየትና ተጠቃሚዎቹ እንዲያውቁት ማድረግ
     የማህበረሰብ የፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ህክምና
    አሰጣጥ ሞዴልን በሚሰጡ መመሪያዎች ላይ በመመርኮዝ
    ተግባራዊ ማድረግ
    መ/ የተሠራውን ሥራ መመዝገብ
    በመጨረሻም የሠራነውን ሥራ መመዝገብና ለሚመለከተው አካል
    ሪፖርት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ እያንዳንዱ አስተባባሪ ድርጅት የራሱ
    የሆነ መረጃ መመዝገቢያና ሪፖርት ማድረጊያ ቅጾች አሉት፡፡ በዚህ
    መልኩ የተሰሩትን ሥራዎች በቅጾቹ መሠረት መዝግቦ ሪፖርት ማድረገ
    ይጠበቃል፡፡
    NEP+
    Tel. +251 116 591 919 / 1818
    P.O. B 789 code 1250
    www.facebook.com/nepplus.nepplus,
    www.nepplus.org, face book Page
    www.facebook.com/Network-of-Networks-of-HIV- Positives-in-Ethiopia